• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ከኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ውይይት አደረጉ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ከኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉኃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ጋር በጽሕፈት ቤታቸው ውይይት አደረጉ። በውይይታቸው ላይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕድ ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በ1940 ዓ/ም የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ሲመሠረት መስራች ከሆኑ አብያተ እምነታት መካከል በቀዳሚ የምትጠቀስ መሆኗን የተሳ ሲሆን በሀገራችን ትውልዳዊና ሀገራዊ ሁለንተናዊ አገልግሎቶች ላይ […]

የቅዱስ ያሬድን ሕይወትና ሥራዎችን የሚያሳይ መንፈሳዊ ፊልም ዝግጅትን አስመልክቶ መግለጫ ተሰጠ

በዋካ ኢንተርቴይመንት የሚሠራውን የቅዱስ ያሬድን ሕይወት እና ሥራዎች የሚያሳይ መንፈሳዊ ፊልም አስመልክቶ ከሊቃውንት ጋር ውይይት በማካሄድ መግለጫ ተሰጠ። የቅዱስ ያሬድን ሕይወት እና ሥራዎች የሚያሳይ መንፈሳዊ ፊልም በዋካ ኢንተርቴይመንት ተሠርቶ በ#EOTCTV ለማሣየት የታቀደውን እቅድ አስመልክቶ የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት እና ዋካ ኢንተርቴይመንት ከያሬዳውያን ሊቃውንት ጋር ውይይት በማድረግ መግለጫ ተሰጠ። መግለጫውን ያቀረቡት ዶክተር አካለወልድ ተሰማ የመገናኛ […]

ለመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አራዳ ጊዮርጊስ) ቤተክርስቲያን ሕንጻ ዕድሳት መላው ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ

ለመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ (አራዳ ጊዮርጊስ) ቤተክርስቲያን ሕንጻ ዕድሳት መላው ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ። የዕድሳቱ ትርጉም ሃይማኖትን፣ ታሪክንና ሀገራዊ ዕሴትን ለትውልድ ማሻገር ነው። ለመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን (አራዳ ጊዮርጊስ) ሕንጻ ዕድሳት በሀገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዲያደርጉ ተጠይቋል ። እድሳቱ ከ157 ሚሊየን ብር በላይ ይጠይቃል የሚል የባለሞያ ጥናት ቀርቧል። ታሪክን […]

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የ2017 ዓ/ም የሥራ ዘመን አፈጻጸምን አስመልክቶ የምስጋናና የዕውቅና መርሐ ግብር አካሄደ

የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የ2017 ዓ/ም የሥራ ዘመን አፈጻጸምን አስመልክቶ የምስጋናና የዕውቅና መርሐ ግብር አካሄደ። መርሐ ግብሩ በዛሬ ዕለት በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የተካሔደ ሲሆን ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ […]

ቤተ ክርስቲያንና መንግሥት ሀገር ጠቀምና ትውልድ ተኮር ሥራዎችን በጋራ መሥራት እንደሚገባቸው ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ

ቤተ ክርስቲያንና መንግሥት ሀገር ጠቀምና ትውልድ ተኮር ሥራዎችን በጋራ መሥራት እንደሚገባቸው ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ገለጹ። በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት በ 2017 ዓ.ም በነበረው የአገልግሎት አፈጻጸም ከክፍለ ከተማው ቤተ ክህነት ጋር በጋራ ሲሠሩ ለነበሩ ባለድርሻ አካላት የምስጋና መርሐ ግብር ነሐሴ 18 በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል የስብከተ ወንጌል አዳራሽ […]

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ የዕረፍት መታሰቢያ ሥርዓተ ጸሎት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ

የብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የዕረፍታቸው መታሰቢያ የጸሎት መርሐ ግብር በመንበረ ጽባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናውኗል። ‎በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ

የብፁዕ ወቅዱስ ዶክተር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ፤ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዚደንት፣ የዓለም ሃይማኖቶች ምክር ቤት ለሰላም የክብር ፕሬዚደንት፣ የዓለም የሰላም አምባሳደር፤ 13ኛ ዓመት ዕረፍት ነሐሴ 10 ቀን 2017 ዓ.ም በመንበረ ጻባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በደማቅ ሁኔታ ይከበራል፡፡ በዚህ ጽሑፍ የቅዱስነታቸው ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም መግባትን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ በረከትና ለአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መመሪያ አስተላለፉ

ብፁዕነታቸው ሱባኤው በሥርዓትና መልስ ሊያስገኝ በሚችል መልኩ መከናወንን እንዳለበት አሳስበዋል። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። በመላው ዓለም የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን አገልጋዮች ምእመናንና ምእመናት እንኳን ለ፳፻፲፯ ዓ/ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም በጤና አደረሳችሁ። “ተመየጡ ኀቤየ ወተሐይዉ በጾም ወበጸሎት ወበርትዕት ሃይማኖት “በጾም በጸሎት በእውነተኛ ሃይማኖትም ወደ እኔ ተመለሱ ትድናላችሁም” ቅዱስ ያሬድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሐዶ ቤተ ክርስቲያን […]

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ.ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የ2017 ዓ/ም የጾመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል። መግለጫው የሚከተለው ነው። መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ፡- በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን፤ በሀገራችን በኢትዮጵያና በመላው ዓለም የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ፡- የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ […]

መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ጊዜ የሰጡትን አባታዊ አገልግሎት አስመልክቶ የምስጋና መርሐ ግብር ተካሄደ

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል እንዲሁም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሰብሳቢ በተገኙበት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ለተመደቡት ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንገሤ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት