• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም መግባትን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ ቃለ በረከትና ለአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መመሪያ አስተላለፉ

ብፁዕነታቸው ሱባኤው በሥርዓትና መልስ ሊያስገኝ በሚችል መልኩ መከናወንን እንዳለበት አሳስበዋል። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን። በመላው ዓለም የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን አገልጋዮች ምእመናንና ምእመናት እንኳን ለ፳፻፲፯ ዓ/ም ጾመ ፍልሰታ ለማርያም በጤና አደረሳችሁ። “ተመየጡ ኀቤየ ወተሐይዉ በጾም ወበጸሎት ወበርትዕት ሃይማኖት “በጾም በጸሎት በእውነተኛ ሃይማኖትም ወደ እኔ ተመለሱ ትድናላችሁም” ቅዱስ ያሬድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሐዶ ቤተ ክርስቲያን […]

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ.ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ የ2017 ዓ/ም የጾመ ፍልሰታ መግባትን አስመልክተው ቃለ ምእዳንና ቡራኬ ሰጥተዋል። መግለጫው የሚከተለው ነው። መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ፡- በስመ ኣብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ኣሓዱ ኣምላክ ኣሜን፤ በሀገራችን በኢትዮጵያና በመላው ዓለም የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ፡- የክብር ባለቤት እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ […]

መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ በነበሩበት ጊዜ የሰጡትን አባታዊ አገልግሎት አስመልክቶ የምስጋና መርሐ ግብር ተካሄደ

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዝዋይ ሐመረ ብርሃን ቅዱስ ገብርኤል ገዳምና ሥራ አመራር መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ የቅዱስ ሲኖዶስ ቋሚ አባል እንዲሁም የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሰብሳቢ በተገኙበት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ለተመደቡት ክቡር መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንገሤ በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስሊቀ ጳጳስ ከሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ውጭ በመመረቂያ ጋውን ጸሎተ ቅዳሴ ላከናወኑት ካህንና የደብሩ አለቃ አስተዳደራዊ ርምጃና ቀኖና ሰጡ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ከሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን ውጭ “በመመረቂያ ጋውን” ጸሎተ ቅዳሴ ላከናወኑት ካህንና የደብሩ አለቃ አስተዳደራዊ ርምጃና ቀኖና ሰጡ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅድሳት መጻሕፍትን መሠረት፣ ትውፊትን እንደመቀነት ቀኖናን እንደአጥር አድርጋ ሥርዐተ አምልኮን እስካሁን ባለመለወጥ እያከናወነች የምትገኝ ድንቅና ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ናት። ይሁንንና መነሻቸው የተለያየ ሆኖ በአሁኑ ጊዜ በሰማይ ሥርዐት በመላእክት ምስጋና […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የውስጥ ቢሮዎች ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመረቀ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የውስጥ ቢሮዎች ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ አቡነ ዲዮስቆሮስ ሊቀ ጳጳስ ቡራኬ ተመረቀ ። የሀገረ ስብከቱ ዋና መሥሪያ ቤት ቀደም ሲል ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ሊቀ ጳጳስ በሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ለመሥራት አቅደው ባይሳካም በኋላ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል በአዲስ አበባ ሀገረ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በአቃቂ ደብረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው በደብሩ የተሠሩት የልማት ሥራዎች አገልግሎት ይሰጡ ዘንድ ባረኩ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በአቃቂ ደብረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው በደብሩ የተሠሩት የልማት ሥራዎች አገልግሎት ይሰጡ ዘንድ ባረኩ። ከብፁዕነቻው ጋር የሀገረ ስብከቱ ዋና ስራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤና የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች አብረው ተገኝተዋል። ብፁዕነታቸው የመጀመሪያውን ጉብኝት በአቃቂ ደብረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ […]

“150 ተፈናቃይ አገልጋዮችን” በተመለከተ ሀገረ ስብከቱ ወደ ሥራ መድቦ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተገለጸ

በቋሚ ቅዱስ ሲኖዶስ የተወሰነላቸውን “150 ተፈናቃይ አገልጋዮችን” በተመለከተ ሀገረ ስብከቱ ወደ ሥራ መድቦ ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ጥረት እያደረገ መሆኑ ተገለጸ። ዛሬ ከሰዓት በኋላ በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ መሪነት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ፣ የዋና ዋና ክፍል ሐላፊዎች፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጆች፣ የሀገረ ስብከቱና […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ በመገንባት ላይ ያለውን የፍል ውሃ መድኃኔዓለም ሕንፃ ቤተክርስቲያን ጎበኙ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ፣ የሐድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነትና የአዲስአበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሐላፊዎች ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰባኪያን ኅብረት ሰብሰቢና ሥራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት በልዩ ሁኔታ በመገንባት ላይ ያለውን የአያት የፍል ውሃ መድኃኔዓለም (አያት ጸበል) ሕንፃ ቤተክርስቲያን ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ብፁዕነታቸው ሕንፃ ቤተክርያኑን ከታች እስከላይ ድረስ የጎበኙ […]

የደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ለነበራቸው አባታዊ ፍቅርና የእረኝነት አገልግሎት ምስጋናውን ገለጸ

የደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ለሰጡት አባታዊ አገልግሎት ምስጋናውን ገለጸ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ለብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀዲያና ስልጤ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደቡብ አፍሪካ ጁሃንስበርግ መንበረ ጵጵስና መድኃኔዓለም ካቴድራል ደማቅ አሸኛኘት መርሐ ግብር ተደረገላቸው። በመርሐ ግብሩ ላይም ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ […]

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ከሀገረ ስብከቱና ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሐላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ትውውቅና ውይይት አካሄዱ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ከሀገረ ስብከቱና ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሐላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ትውውቅና ውይይት አካሔዱ ። ግንቦት 15/2017 ዓ/ም በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው መመደባቸው የሚታወስ ነው። በመሆኑም ብፁዕነታቸው በዛሬው ከሀገረ ስብከቱና ከክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሐላፊዎችና ሠራተኞች ጋር ትውውቅና ውይይት ያደረጉ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን