• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የታኅሣሥ ፫ በዓታ ለማርያም ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል

ከተከበሩ የተከበረች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ድንግል ማርያም በሦስት ዓመቷ ከእናቷና ከአባቷ ተለይታ ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት “በዓታ ለማርያም” በዓል ታኅሣሥ 3 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በጥንታዊቷ ታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ሊቃውንት እና በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ኦርቶዶክሳውያን በተገኙበት ተከብሯል። ፎቶ eotc tv […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ለመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዕድሳት የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ለመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዕድሳት ማስፈጸሚያ የገንዘብ ድጋፍ አደረጉ። በዕድሳት ላይ የሚገኘው የመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከፍጻሜ ለማድረስ መላው ኦርቶዶክሳዊ ርብርብ እያደረገ ይገኛል። የዕድሳቱን ሂደት በተመለከተ ከፍተኛ ክትትል እያደረጉ የሚገኙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ […]

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የራሱን ቢሮ ለመገንባት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንደተረከበ ተገለጸ

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የራሱን ቢሮ ለመገንባት የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንደተረከበ ተገለጸ ። በሥሩ ፴፭ አብያተ ክርስቲያናት ያሉት የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የቤተ ክርስቲያን አደራ በመጠበቅ ዘመኑን የዋጀ አሠራር ተገልባራዊ ለማድረግ የተለያዩ ሥራዎችን እየሠራ እንደሚገኝ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቱ ገልጿል። ከነዚህ ሥራዎች መካከል ለክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቱ መገልገያ ቢሮ የሚሆን […]

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የ2017 ዓ/ም የአእላፋት ዝማሬ የጥናት መርሐ ግብርን አስጀመሩ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የ2017 ዓ/ም የአእላፋት ዝማሬ የጥናት መርሐ ግብርን አስጀመሩ። የጌታችንን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን የልደት በዓል ምክንያት በማድረግ በኢትዮጵያው ጀንደረባው ትውልድ የሚዘጋጀው የእላፋት ዝማሬ በ2016 ዓ/ም የተጀመረ ሲሆን በርካታ ኦርቶዶክሳውያን በምስጋናው ተባብረዋል። የዝማሬ መርሐ ግብሩ በዚህ ዓመት የሚቀጥል ሲሆን ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ […]

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በሀገረ ስብከቱ በሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተቋማዊ የሆነ የበይነ መረብ ሚዲያ እንዲቋቋም መመሪያ አስተላለፉ።

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በሀገረ ስብከቱ በሁሉም አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ተቋማዊ የሆነ የበይነ መረብ ሚዲያ እንዲቋቋም መመሪያ አስተላለፉ። ብፁዕነታቸው ይሄን ያሉት “መገናኛ ብዙኃን ለቤተ ክርስቲያን ተሌእኮ ” ቀሚሙም መሪ ቃል ሀገረ ስብከቱ ከTakeoff Digital ከተባለ ድርጅት ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የሦስት ቀናት ሥልጠና መርሐ ግብር ተዘጋጀው ላይ ነው። ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት “መገናኛ ብዙኃን ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ” በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው የሦስት ቀናት ሥልጠና ተጠናቀቀ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት “መገናኛ ብዙኃን ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ” በሚል መሪ ቃል ያዘጋጀው የሦስት ቀናት ሥልጠና ተጠናቀቀ። ሀገረ ስብከቱ Takeoff Digital ከተባለና መቀመጫውን ዱባይ ያደረገ በcyber Security and Artifical Intelligence ከሚሠራ ድርጅት ጋር በመተባበር በማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች አጠቃቀም ዙሪያ በተመለከተ ለሦስት ተከታታይ ቀናት ከሁሉም ገዳማትና አድባራት ለተውጣጡ በርካታ ቁጥር ላላቸው ሠልጣኞት ሥልጠናው ተሰጥቷል። ሥልጠና በብፁዕነታቸው […]

የመካነ መቃብራት አያያዝና አጠቃቀም ትኩረት እንደሚሹ ተገለጸ።

የሰው ልጆች ምድራዊ ቆይታችንን አጠናቀን ከዚህ ዓለም በሞት በምንለይበት ወቅት ቤተ ክርስቲያን አስከሬናችንን ተቀብላ በክብር በቤተክርስቲያን ቅፅር ግቢ ውስጥ ታሳርፈዋለች። በተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ የሚገኙ መካነ መቃብራት በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ አስከሬኖችን ይዘው የሚገኙ ቢሆንም በተደጋጋሚ ጊዜ ከምእመናን ከሚነሱ ቅሬታዎች መካከል ለቦታው ልዩ ትኩረት ካለመስጠት የተነሳ የፅዳት ችግር እና የተለያዩ አላስፈላጊ ድርጊት እየተፈፀመባቸው መሆኑ ይገኛል። ስማቸውን […]

የሰባክያነ ወንጌል ኅብረት ጥሪ

ለታላቅ የምሥራች ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ “በወንጌልም ማኅበረተኛ እሆን ዘንድ ስለ ወንጌል ሁሉን አደርጋለሁ።” ፩ኛ ቆሮንቶስ ፱፥፳፫ የፊታችን ቅዳሜ ጥቅምት 30/2017 ዓ.ም በቦሌ ደብረ ሳሌም መድኃኔዓለም ካቴድራል ትልቁ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ከቀኑ 7፡00 ሰዓት ጀምሮ በአ/አ ሀገረ ስብከት የሰባክያነ ወንጌል ኅብረትን በማስመልከት የምስጋናና የዕውቅና መርሐግብር ላይ መላው ኦርቶዶክሳውያን ተገኝታችሁ የደስታ ቀናችንን በጋራ እናክብር በማለት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡ በዕለቱም፡- […]

“ሰላም ከአንገት በላይና ዝም ላለማለት ያህል የምንናገረው ሳይሆን ዋጋ ከፍለን የምናመጣው ነው”

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ጥቅምት ፳፭/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የሰላም ሚኒስቴር ዛሬ ጥቅምት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ባዘጋጀው ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ላይ መልእክት አስተላልፈዋል። በመልእክታቸውም “ሰላም ከአንገት በላይና ዝም ላለማለት ያህል የምንናገረው ሳይሆን ዋጋ ከፍለን […]

የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲሆን በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት ምልዓተ ጉባኤው ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ መደበኛ ስብሰባውን ሲያካሂድ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን