• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ትናንት ጥር ፲፯/፳፻፲፯ ዓ/ም ሐዋርያዊ ጉብኝት አደረጉ። በሐዋርያዊ ጉብኝታቸው ደብሩ ለሰንበት ትምህርት ቤት መገልገያ እንዲሆን የሚገነባው ባለሁለት ወለል (G+2) ሕንጻ መሠረት ድንጋይ ባርከው አስቀምጠዋል። ከዚሁ ጋር ደብሩ ለጸበል አገልግሎት እንዲሰጡ ገንብቶ ያጠናቀቃቸውን 12 ክፍሎች መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል። ብፁዕነታቸው በደብሩ […]

የከተራ እና የጥምቀት እንዲሁም የቃና ዘገሊላ በዓላት በሰላም መከበራቸውን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ

“ይትባረክ እግዚአብሔር፣ አቡሁ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ፤ ዘባረከነ በኩሉ በረከተ መንፈስ ቅዱስ ዘበሰማያት በክርስቶስ ኢየሱስ፣ በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን ፤ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ” (ኤፌ.1፥3/ ብርሃነ ዓለም እየተባለ የሚጠራው ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኤፌሶን መልእክቱ የተባረክንበት በረከት ምንያህል ትልቅ መሆኑንና ባረኪው እግዚአብሔር በልጁ እንደቀሰን ሲናገር “በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን […]

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመንፈሳዊ ሥርዓትና በሰላም መከበራቸውን አስመልክተው የምስጋና መልእክት አስተላለፉ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመንፈሳዊ ሥርዓትና በሰላም መከበራቸውን አስመልክተው የምስጋና መልእክት አስተላለፉ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን በልዩ ሥርዓትና በዐደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በእጅጉ ተጠቃሾች ናቸው። በዓሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአርአያነትና የሰው ልጆችን የዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄዱንና መጠመቁን እንዲሁም ጌታ ከገዳመ […]

የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር ፲፪ ቀን በ UNESCO እንዲመዘገብና በኢትዮጵያም ብሔራዊ በዓል እንዲሆን በድጋሜ ተጠየቀ

የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር ፲፪ ቀን በዩኔስኮ እንዲመዘገብና በኢትዮጵያም ብሔራዊ በዓል እንዲሆን በድጋሜ ተጠየቀ። በየዓመቱ ከጥምቀት በዓል ቀጥሎ የሚከበረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ሥጋዌው በዓደባባይ ካሳያቸው ተአምራት መካከል የመጀመሪያ የሆነው በቃና ዘገሊላ ሠርግ ላይ ውኃውን ወደ ወይን የለወጠበት የተአምር በዓል ቃና ዘገሊላ በሚል ይከበራል። በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ባለችበት ሁሉ […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጥምቀት በዓል ዓላማውን በጠበቁ መልኩ በሰላም መከበሩን የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ገለጹ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጥምቀት በዓል ዓላማውን በጠበቁ መልኩ በሰላም መከበሩን የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ገለጹ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያችን በየዓመቱ በዓደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል አንድ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ነው። በዓሉ በዚህ ዓመት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በ250 አብያተ ክርስቲያናት በ66 አብሕርተ ጥምቀት የተከበረ ሲሆን በካህናት ምስጋና […]

“የእግዚአብሔር የዝግጅት ጥሪ ዘላዓለማዊ ሕይወትን ለማደል ሆኖ ሳለ የተጠበቀው ዝግጅት ግን ከሰው እየታየ ኣይደለም” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና የተከበራችሁ የበዓሉ በረከት ተሳታፊዎች በአጠቃላይ በቅርብና በሩቅ ሆናችሁ የየ2017 ዓ.ም በዓለ ጥምቀት እያከበራችሁ የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ፣ በመጠመቁ የክዋኔ ልጅነቱን አስመስክሮ የጸጋ ልጆች እንድንሆን ያበቃንን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመት ምሕረት የጥምቀተ ክርስቶስ በዓል […]

የበዓለ ጥምቀት ዋዜማ ከተራ በዓል በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በተገኙበት ተከብሯል

በየዓመቱ የሚከበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምተቅ ዋዜማ ከተራ በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ሮእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል። በዓሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሰስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄዱም የሚታሰብበት በመሆኑ ታቦታቱ ከመንበረ ክብራቸው ወደ ተዘጋጀው የባሕረ ጥምቀት […]

“ግበሩኬ እንከ ፍሬ ሠናየ ዘይደልወክሙ ለንስሓ ፤ እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ” ማቴ ፫፥፰

ጥምቀት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተፈጸመልን የድኅነት ምልክታችን፣ መሸጋገሪያችን እና ጠላትን ድል መንሻችን ነው። ሐዋርያው እንደተናገረ ከመድኃኒታችን ጋር በትንሣኤው ተባባሪ ለመሆን በጥምቀት መቀበር ተገቢ ነውና (ቆላ ፪፥፲፪) ቤተ ክርስቲያናችን የዕዳ ደብዳቤያችን የተቀደደበትን፣ ልዑል አምላካችን በፍፁም ትህትና በፍጡር እጅ የተጠመቀበትን አብነት አድርገን እንድንመለከት ታስተምረናለች። የበረሃው ኮከብ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀት በሚያጠምቅበት በዚያን ወራት ከክፉ ሥራ […]

የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የ 2017 ዓ.ም በዓለ ጥምቀትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት የተሰጠ መግለጫ

“አንሰኬ አጠምቀክሙ በማይ ለንስሐ፣ ወእምድኅሬየሰ ይመጽእ ውእቱ ይጸንዕ እምኔየ፣ ዘኢይደልወኒ እጹር አሣእኖ፣ ውእቱሰ ያጠምቀክሙ በመንፈስ ቅዱስ ወበእሳት፣ እኔ ለንስሐ በውሀ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል”፤ (ማቴ.3:11) በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጆች ምእመናንና ምእመናት ፦ መጋቤ ዓለማት፤ ፈጣሬ ፍጥረታት […]

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት መሪዎችና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ከክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚና ጸጥታ ዘርፍ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ በቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት መሪዎችና አድባራት አስተዳዳሪዎች ከክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚና ጸጥታ ዘርፍ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ። በየዓመቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ በ65 የታቦታት ማደሪ ባሕረ ጥምቀት የሚከበር ሲሆን በዓሉ በሰላምና ዓላማውን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል። በዛሬው ዕለት የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ና […]

የቅዱስነታቸው ቃለ በረከት

የስብሰባው አቋም መግለጫ

የሕግ መጻሕፍት ትሩፋት

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲሱ የሀገረ ስብከቱ አሰራርን አስመልክተው ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት ቀለ መጠይቅ

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲሱ የሀገረ ስብከቱ አሰራርን አስመልክተው ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉትን ቀለ መጠይቅ ይመልከቱ ሌሎችም እንዲያዩት በፌስ ቡክ፣ በቴሌግራም፣ በዩቲዩብ….. ሼር ያድርጉ!!!

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዐብይ ጾም መግቢያን አስመልክተው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት

መልካም አስተዳደር ለቤተክርስቲያን አገልግሎትና ልማት በሚል ርዕስ በሊ/ት በድሉ አሰፋ ዓለማየሁ በሀገረ ስብከቱ በተዘጋጀው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተካደው ጉባኤ ላይ ተሳታፊዎች የቀረበ ጥናታዊ ጽሑፍ

መ/ር አካለወልድ ተሰማ የአ/አ/ሀ/ስ/ ዋና ስራ አስኪያጅ የከተራ እና ጥምቀት በዓል በዓለም ምን እንደሚመስል ሃይማኖታዊ እንድምታ እና ሥርዓቱ ምንድን ነው ? በሚል ርዕስ የሰጡትን ማብራሪያ ይከታተሉ

ማስታወቂያ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን