• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የበዓለ ጥምቀት ዋዜማ ከተራ በዓል በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በተገኙበት ተከብሯል

በየዓመቱ የሚከበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምተቅ ዋዜማ ከተራ በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ሮእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል። በዓሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሰስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄዱም የሚታሰብበት በመሆኑ ታቦታቱ ከመንበረ ክብራቸው ወደ ተዘጋጀው የባሕረ ጥምቀት […]

“ግበሩኬ እንከ ፍሬ ሠናየ ዘይደልወክሙ ለንስሓ ፤ እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ” ማቴ ፫፥፰

ጥምቀት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተፈጸመልን የድኅነት ምልክታችን፣ መሸጋገሪያችን እና ጠላትን ድል መንሻችን ነው። ሐዋርያው እንደተናገረ ከመድኃኒታችን ጋር በትንሣኤው ተባባሪ ለመሆን በጥምቀት መቀበር ተገቢ ነውና (ቆላ ፪፥፲፪) ቤተ ክርስቲያናችን የዕዳ ደብዳቤያችን የተቀደደበትን፣ ልዑል አምላካችን በፍፁም ትህትና በፍጡር እጅ የተጠመቀበትን አብነት አድርገን እንድንመለከት ታስተምረናለች። የበረሃው ኮከብ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀት በሚያጠምቅበት በዚያን ወራት ከክፉ ሥራ […]

የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የ 2017 ዓ.ም በዓለ ጥምቀትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት የተሰጠ መግለጫ

“አንሰኬ አጠምቀክሙ በማይ ለንስሐ፣ ወእምድኅሬየሰ ይመጽእ ውእቱ ይጸንዕ እምኔየ፣ ዘኢይደልወኒ እጹር አሣእኖ፣ ውእቱሰ ያጠምቀክሙ በመንፈስ ቅዱስ ወበእሳት፣ እኔ ለንስሐ በውሀ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል”፤ (ማቴ.3:11) በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጆች ምእመናንና ምእመናት ፦ መጋቤ ዓለማት፤ ፈጣሬ ፍጥረታት […]

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት መሪዎችና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ከክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚና ጸጥታ ዘርፍ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ በቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት መሪዎችና አድባራት አስተዳዳሪዎች ከክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚና ጸጥታ ዘርፍ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ። በየዓመቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ በ65 የታቦታት ማደሪ ባሕረ ጥምቀት የሚከበር ሲሆን በዓሉ በሰላምና ዓላማውን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል። በዛሬው ዕለት የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ና […]

ዓመታዊ የቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓልና የቤተ መቅደሱ መታደስ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከበረ

ዓመታዊው የአጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓልና የቤተ መቅደሱ መታደስ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከበረ። የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በትናትናው ዕለት የቤተ መቅደሱን መታደስ በዓል የተከበረ ሲሆን በዛሬ ዕለትም የቅድሥት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከብሯል። በበዓሉ ላይ የካቴድራሉ ሊቃውንት ማኅሌታውያን “ዮም መላእክት ይየብቡ ወሊቃነ መላእክት […]

የጻድቁ የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ በዓለ ዕረፍት በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተከበረ

የጻድቁ የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ በዓለ ዕረፍት በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተከበረ። በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደኖሩ የሚነገርላቸው ጻድቁ አቡነ ሊባኖስ ትውልዳቸው ሮም ሲሆን በግብጽ፣ ኢትዮጵያና ኤርትራ እየተዘዋወሩ በብርቱ ቅዱስን ወንጌል በሕይወት እግዚአብሔርን በእውነት አግልግለዋል። ጻድቁ አቡነ ሊባኖስ ምንኩስናን ከአባ ጳኩሚስ የተቀበሉ ሲሆን በኢትዮጵያና በኤርትራ የተለያዩ ገዳማትን […]

“የወለዱትን ማሳደግ ከባድ በሆነበት በዚህ ዘመን ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሕጻናትን ሰብስቦ ማሳደግ ሀገራዊና መንፈሳዊ ኃላፊነትን መወጣት ነው”። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ

“የወለዱትን ማሳደግ ከባድ በሆነበት በዚህ ዘመን ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ሕጻናትን ሰብስቦ ማሳደግ ሀገራዊና መንፈሳዊ ኃላፊነትን መወጣት በማለት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ገለጹ። ቅዱስነታቸው ይህንን ያሉት በዛሬ ዕለት የሰበታ ጌቴሴማኒ ቤተ ደናግል ወጠባባት የእናቶች ገዳምንና በዚያ የሚያድጉ ሕጻናትን በመጎብኘት ቡራኬ በሰጡበት መርሐ ግብር […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክተው አባታዊ የሰላም ጥሪ አስተላለፉ። ቅዱስነታቸው በመልዕክታቸው እንደገለጹት የሰላም ትርጉሙ ተረጋግቶ መኖር፣ ወደ ዓላማ ፍጻሜ መድረስ፣ መርቆ ማለፍ ነው። ካሉ በኋላ ወልዶ ለመሳም፣ አሳድጎ ለመዳር፣ ዐርፍተ ዘመን የገታቸውን በክብር ለመሸኘት ሰላም አስፈላጊ ነው ።ብለዋል። አያይዘውም እስካሁን […]

የ፳፻፲፯ ዓ/ም በዓለ ልደት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ እንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ተከናወነ

በየዓመቱ የሚከናወነው ይህ የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ለቤተ ክርስቲያናችን ርእሰ መንበር ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ለሆኑት አባት የሚደረግ ሥርዐት ነው። መርሐ ግብሩ ከበዓለ ልደት በተጨማሪ በበዓለ ትንሣኤ እንዲሁም በዘመን መለወጫ የሚካሔድ ነው። በዚህ በ፳፻፲፯ ዓ/ም በዓለ ልደት ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የእንኳን አደረሰዎ መርሐ […]

“ይእዜ አስተርአየ እግዚአብሔር ዮም እምቅድስት ድንግል፤ ዛሬ እግዚአብሔር ከቅድስት ድንግል በሥጋ ተወልዶ ታየ” ሃይ.አበው ዘቴዎዶጦስ

ተወዳጅ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቼ እንኳን ለ፳፻፲፯ ዓ.ም የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ ! አባቶቻችን ሊቃውንት እንዳስተማሩን በዛሬው ዕለት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተዋረደውን የእኛን ሥጋ በመዋሐድ ከወድቀት ወደ ከፍታ፤ ከመዋረድ ወደ ክብር ከፍ አድርጎናል። ሁሉን ቻይ የሆነው አምላካችን ከአዳም ባሕርይ ከተገኘች እመቤታችን እንበለ ዘርዕ ነፍስንና ሥጋን ተዋሕዶ አከበረን። ለአንዲት ሰከንድ ቆም ብለን […]

የቅዱስነታቸው ቃለ በረከት

የስብሰባው አቋም መግለጫ

የሕግ መጻሕፍት ትሩፋት

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲሱ የሀገረ ስብከቱ አሰራርን አስመልክተው ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት ቀለ መጠይቅ

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲሱ የሀገረ ስብከቱ አሰራርን አስመልክተው ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉትን ቀለ መጠይቅ ይመልከቱ ሌሎችም እንዲያዩት በፌስ ቡክ፣ በቴሌግራም፣ በዩቲዩብ….. ሼር ያድርጉ!!!

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዐብይ ጾም መግቢያን አስመልክተው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት

መልካም አስተዳደር ለቤተክርስቲያን አገልግሎትና ልማት በሚል ርዕስ በሊ/ት በድሉ አሰፋ ዓለማየሁ በሀገረ ስብከቱ በተዘጋጀው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተካደው ጉባኤ ላይ ተሳታፊዎች የቀረበ ጥናታዊ ጽሑፍ

መ/ር አካለወልድ ተሰማ የአ/አ/ሀ/ስ/ ዋና ስራ አስኪያጅ የከተራ እና ጥምቀት በዓል በዓለም ምን እንደሚመስል ሃይማኖታዊ እንድምታ እና ሥርዓቱ ምንድን ነው ? በሚል ርዕስ የሰጡትን ማብራሪያ ይከታተሉ

ማስታወቂያ

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቅያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከዚህ በታች በተጠቀሱት ክፍት የሥራ መደቦች ላይ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን