• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመንፈሳዊ ሥርዓትና በሰላም መከበራቸውን አስመልክተው የምስጋና መልእክት አስተላለፉ

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በመንፈሳዊ ሥርዓትና በሰላም መከበራቸውን አስመልክተው የምስጋና መልእክት አስተላለፉ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን በልዩ ሥርዓትና በዐደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል የጥምቀትና የቃና ዘገሊላ በዓላት በእጅጉ ተጠቃሾች ናቸው። በዓሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአርአያነትና የሰው ልጆችን የዕዳ ደብዳቤ ለመደምሰስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄዱንና መጠመቁን እንዲሁም ጌታ ከገዳመ […]

የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር ፲፪ ቀን በ UNESCO እንዲመዘገብና በኢትዮጵያም ብሔራዊ በዓል እንዲሆን በድጋሜ ተጠየቀ

የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር ፲፪ ቀን በዩኔስኮ እንዲመዘገብና በኢትዮጵያም ብሔራዊ በዓል እንዲሆን በድጋሜ ተጠየቀ። በየዓመቱ ከጥምቀት በዓል ቀጥሎ የሚከበረው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ሥጋዌው በዓደባባይ ካሳያቸው ተአምራት መካከል የመጀመሪያ የሆነው በቃና ዘገሊላ ሠርግ ላይ ውኃውን ወደ ወይን የለወጠበት የተአምር በዓል ቃና ዘገሊላ በሚል ይከበራል። በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያናችን ባለችበት ሁሉ […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጥምቀት በዓል ዓላማውን በጠበቁ መልኩ በሰላም መከበሩን የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ገለጹ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የጥምቀት በዓል ዓላማውን በጠበቁ መልኩ በሰላም መከበሩን የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ገለጹ። ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያችን በየዓመቱ በዓደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል አንድ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ነው። በዓሉ በዚህ ዓመት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በ250 አብያተ ክርስቲያናት በ66 አብሕርተ ጥምቀት የተከበረ ሲሆን በካህናት ምስጋና […]

“የእግዚአብሔር የዝግጅት ጥሪ ዘላዓለማዊ ሕይወትን ለማደል ሆኖ ሳለ የተጠበቀው ዝግጅት ግን ከሰው እየታየ ኣይደለም” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ

መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና የተከበራችሁ የበዓሉ በረከት ተሳታፊዎች በአጠቃላይ በቅርብና በሩቅ ሆናችሁ የየ2017 ዓ.ም በዓለ ጥምቀት እያከበራችሁ የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ፣ በመጠመቁ የክዋኔ ልጅነቱን አስመስክሮ የጸጋ ልጆች እንድንሆን ያበቃንን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመት ምሕረት የጥምቀተ ክርስቶስ በዓል […]

የበዓለ ጥምቀት ዋዜማ ከተራ በዓል በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ በተገኙበት ተከብሯል

በየዓመቱ የሚከበረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምተቅ ዋዜማ ከተራ በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ሮእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል። በዓሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሰስ ክርስቶስ በዮሐንስ እጅ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ መሄዱም የሚታሰብበት በመሆኑ ታቦታቱ ከመንበረ ክብራቸው ወደ ተዘጋጀው የባሕረ ጥምቀት […]

“ግበሩኬ እንከ ፍሬ ሠናየ ዘይደልወክሙ ለንስሓ ፤ እንግዲህ ለንስሐ የሚገባ ፍሬ አድርጉ” ማቴ ፫፥፰

ጥምቀት በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተፈጸመልን የድኅነት ምልክታችን፣ መሸጋገሪያችን እና ጠላትን ድል መንሻችን ነው። ሐዋርያው እንደተናገረ ከመድኃኒታችን ጋር በትንሣኤው ተባባሪ ለመሆን በጥምቀት መቀበር ተገቢ ነውና (ቆላ ፪፥፲፪) ቤተ ክርስቲያናችን የዕዳ ደብዳቤያችን የተቀደደበትን፣ ልዑል አምላካችን በፍፁም ትህትና በፍጡር እጅ የተጠመቀበትን አብነት አድርገን እንድንመለከት ታስተምረናለች። የበረሃው ኮከብ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የንስሐ ጥምቀት በሚያጠምቅበት በዚያን ወራት ከክፉ ሥራ […]

የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የ 2017 ዓ.ም በዓለ ጥምቀትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት የተሰጠ መግለጫ

“አንሰኬ አጠምቀክሙ በማይ ለንስሐ፣ ወእምድኅሬየሰ ይመጽእ ውእቱ ይጸንዕ እምኔየ፣ ዘኢይደልወኒ እጹር አሣእኖ፣ ውእቱሰ ያጠምቀክሙ በመንፈስ ቅዱስ ወበእሳት፣ እኔ ለንስሐ በውሀ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል”፤ (ማቴ.3:11) በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልጆች ምእመናንና ምእመናት ፦ መጋቤ ዓለማት፤ ፈጣሬ ፍጥረታት […]

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት መሪዎችና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ከክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚና ጸጥታ ዘርፍ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ

በዓለ ጥምቀትን አስመልክቶ በቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት መሪዎችና አድባራት አስተዳዳሪዎች ከክፍለ ከተማው ሥራ አስፈጻሚና ጸጥታ ዘርፍ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገለጸ። በየዓመቱ የሚከበረው የጥምቀት በዓል በአዲስ አበባ በ65 የታቦታት ማደሪ ባሕረ ጥምቀት የሚከበር ሲሆን በዓሉ በሰላምና ዓላማውን በጠበቀ መልኩ እንዲከበር ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገ እንደሚገኝ ይታወቃል። በዛሬው ዕለት የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ና […]

ዓመታዊ የቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓልና የቤተ መቅደሱ መታደስ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከበረ

ዓመታዊው የአጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓልና የቤተ መቅደሱ መታደስ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በድምቀት ተከበረ። የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በትናትናው ዕለት የቤተ መቅደሱን መታደስ በዓል የተከበረ ሲሆን በዛሬ ዕለትም የቅድሥት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከብሯል። በበዓሉ ላይ የካቴድራሉ ሊቃውንት ማኅሌታውያን “ዮም መላእክት ይየብቡ ወሊቃነ መላእክት […]

የጻድቁ የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ በዓለ ዕረፍት በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተከበረ

የጻድቁ የአቡነ ሊባኖስ ዘመጣዕ በዓለ ዕረፍት በእንጦጦ ሐመረ ኖኅ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ገዳም ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተከበረ። በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደኖሩ የሚነገርላቸው ጻድቁ አቡነ ሊባኖስ ትውልዳቸው ሮም ሲሆን በግብጽ፣ ኢትዮጵያና ኤርትራ እየተዘዋወሩ በብርቱ ቅዱስን ወንጌል በሕይወት እግዚአብሔርን በእውነት አግልግለዋል። ጻድቁ አቡነ ሊባኖስ ምንኩስናን ከአባ ጳኩሚስ የተቀበሉ ሲሆን በኢትዮጵያና በኤርትራ የተለያዩ ገዳማትን […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን