• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

6

የ2005ዓ.ም የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከበረ

እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥመቀት በሰላም በጤና በሕይወት አደረሳችሁ፡፡                                   በመ/ር ዘሩ እና በመ/ር ኃይሉ በየዓመቱ ጥር 10 እና 11 የሚከበረው የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥመቀት በገነተ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን መሪነት ከ13 ታቦታት በላይ በሚያድሩበት በጃን ሜዳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ […]

5.3

ዓመታዊው የዓጋዓዝተ ዓለም ሥላሴ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ

                            እንኳን ለአብርሃሙ ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም በጤና በሕይወት አደረሳችሁ፡፡                                                                በመ/ር ዘሩ እና በመ/ር ኃይሉ ‹‹እመ እግዚአብሔር ኢሐነፀ ቤተ ከንቶ ይፃምው እለ የሃንፁ›› ‹‹እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ ግንበኞቹ በከንቱ ይደክማሉ›› መዝ 126፡1 ይህን የታላቁን ነቢይ ቃል ለመነሻነት የተመረጠው ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን የሚከበረው የአጋዕዝተ ዓለም ሥላሴ በዓለ ንግሥን ምክንያት ለመግለፅ ነው፡፡ ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ዳዊት […]

5.1

የምዕራብ፤የምስራቅና የደቡብ አዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ስለጥምቀት በዓል አከባበርና አጠቃላይ ስለስራ ሁኔታ ከአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ሠራተኞች ጋር የውይይት መርሃ ግብር ተካሄደ

                                                           በመ/ር ዘሩ እና በመ/ር ኃይሉ ክቡር መልአከ ጽዮን አባ ኅሩይ ወንድይፍራው ስብሰባውን ሲመሩ ቀደም ሲል የሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በታኅሣሥ 26/05 ዓ.ም በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ ስብሰባ መካሄዱንና ወሳኝና ወቅታዊ የሆኑ መመሪዎች እንደተላለፉ በወቅቱ በድህረ ገፃችን ላይ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ከሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ቀጥሎ ጥር 4/05/05 ዓ.ም ሰብሰባ ያካሄደው የምዕራብ አዲስ […]

03

የልደት በዓል በሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድምቅት ተከበረ

                                                                                      በመ/ር ዘሩ እና ኃይሉ                      እነሆ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኀኒት ተወልዶላችኋል ሉቃ.2፥11 እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ፡፡ የጌታችን የአምላካችን የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ታላላቅ በዓላቶች መካከል አንዱ ሲሆን ሁሌ በየዓመቱ ታኅሣሥ 29 እንደሚከበር ይታወቃል፡፡ እንደ ተለመደው የዘንድሮ በዓልም መከበር የጀምረው ከዋዜማው 12.00 ሰዓት […]

4.1

ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ ተወልዶላችኋል ሉቃ.2÷11

                                          በመ/ር ኃይሉ እና ዘሩ

4.1

እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቀን አቆጣጠር ቀመር አሁን በ2ዐዐ5 ዓ.ም የምናከብረው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የልደት ዘመን 2ዐዐ5 ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡

እግዚአብሔር አዳምን በ7ኛ ቀን ሔዋንን ደግሞ በ14ኛ ቀን ከፈጠረ በኋላ በገነት እግዚአብሔር አምላካቸውን እያመሰገኑ እንዲኖሩ ቢያስቀምጣቸው እነርሱ ግን ባለመታዘዝና ወደ መመራመር በመግባት ከእግዚአብሔር ተለይተው ከገነት በመውጣት እሾህና አሜኬላ ወደምታፈራው ምድር ወርደው እንዲኖሩና ከእነርሱ የተገኙት ልጆቻቸውም የዚህ ገፈት ቀማሽ እንዲሆኑ ተበይኖባቸዋል፡፡ አዳምም ታሪክ እንደሚነግረን በተለያዩ ጊዜያት ወደ ነበረበት ለመመለስ ጥረት ቢያደርግም የሳጥናኤልን ጥበብ ማለፍ አቅቶት ሳይሳካለት በመቅረቱ እግዚአብሔር ጥረቱን ተመልክቶ ወደ ተባረርክበት እና ወዳሰብክበት ገነት መግባት ቢያቅትም አንተ ድል መንሳት ባቃተህ ሥጋ ተዋሕጄ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው በማለት ቃል ገብቶለታል፡፡ ከዚህ ቃል ኪዳንም የተነሳ የአዳም ልጆች እና ልጅ ልጆች አቤቱ እጅህን ከአርያም ልከህ አድነን፣ ጨለማችን ይብራ፣ እስራታችን ይፈታ ይበጠስ እያሉ ያለቅሱ ይጮኹ ነበር፤ በየዓመቱም ሱባኤ በመቁጠር እየፆሙ ይፀልዩ ነበር፡፡ እርሱም የነቢያት የአባቶቻችንን ጩኸት በመስማት ቀኑ በደረሰ ጊዜ የሸክሙን ቀንበር፣ የአስጨናቂውን ዘንግ፣ ለመስበር፣ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል የተዘረጋውን የጠብ ግርግዳ ለመቅረፍ፣ በጨለማ ለሚኖረውም ሕዝብ ብርሃን ለመስጠትና ለመሆን፣ ነቢያት የናፈቋትን የማዳኑን ዕለት ለማሳየት በሉቃስ ወንጌል እና በሌሎቹም ወንጌላት ላይ እንደተጠቀሰው በእንግድነት ለቆጠራ በሄዱበት በዳዊት ከተማ

abune_nathnael

ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የገና 2005ዓ.ም በዓለ ልደት ምክንያት በማድረግ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን                                                                                                       በመ/ር ዘሩ እና ኃይሉ በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችኹ ፣ በሕማም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችኹ ፣ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ኾናችኁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት እንኳን ለ2005 ዓ.ም የጌታችን፣ የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዐለ […]

img_0011

በሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከገዳማትና አድባራት ሠራተኞች ጋር የትውውቅ መርሃ ግብር ተካሄደ

በመ/ር ዘሩ እና ኃይሉ   ክቡር መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ ስብሰባውን ሲመሩ ታኅሣሥ 26/005 ዓ.ም በአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ ከጠዋቱ 3.00 ሰዓት ጀምሮ መርሃ ግብሩ የተካሄደ ሲሆን በትውውቅ መርሀ ግብሩ ላይ ክቡር መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ የሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅን ጨምሮ ሁሉም የሀገረ ስብከቱ የክፍል ሃላፊዎቹና ሠራተኞች እንዲሁም የገዳማትና […]

img_0002

በአ.አ.አ.ስ .ግ. ፈንድ 7ኛ ዙር ፕሮጀክት የ4ኛ፤ሁ2ኛ ፤ 3ኛና እሩብ ዓመት የድጋፍ እርዳታና በጥቃቅንና አነስተኛ ለሚደራጁ ስልጠና ተካሄደ

                                                                                                  በመ/ር ዘሩ እና ኃይሉ መ/ር ዮናስ ፍቅሩ ፕሮግራሙን ሲመራ   በአዲስ አበባ አህጉረ ሰብከት የግሎባል ፈንድ 7ኛ ፕሮጀክት ቅ/ጽ/ቤት ላለፉት አራት ዓመታት ለወላጅ አጥና በችግር የተጋለጡ ህፃናት ድጋፍ እና እንክብካቤ ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ በዚሁም በርካታ ተጠቃሚዎችን መርዳት ተችሏል፡፡ እ.አ.አ 2012 የበጀት ዓመት የሁለተኛ እና የሶስተኛ እሩብ አመት ስራዎች በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ለ465 ዜጎች የምግብ የልብስ […]

2

በኢ.ኦ.ተ.ቤ.ክ. በየዓመቱ የሚከበረው ዓመታዊው የኃያሉ መልአክ የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግሥ በድምቀት ተከበረ

ታኅሣሥ 19 ቀን 2005 ዓ.ም.                     በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ በመጀመሪያ እንኳን ለኃያሉ መልአክ ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ አደረሰን እንላለን፡፡ እኛ የምናመልከው አምላክ ኪሚነደው ከእሳቱ እቶን ያድነን ዘንድ ይችላል፡፡ ት.ዳን.3፥17 በየዓመቱ ታህሳስ 19 ቀን የሚከበረው ዓመታዊው የኃያሉ የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግሥ በዚህ ዓመትም እጅግ በጣም በደመቀ ሁኔታ ተከብሮ […]

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የጋራ ልምድ ልውውጥ ጉባኤ ተካሄደ

                         በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እና በግብፅ ኮብፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በጋራ ትብብር በምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ላይ ሰፊ የልምድ ልውውጥ መርሀ ግብር በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተካሂዷል፡፡ይህ ጉባኤ ከታኅሣሥ 11-15 ቀን 2005 ዓ.ም. ለአምስት ተከታታይ ቀናት ልምድ ልውውጡ የተከናወነ ሲሆን በአምስቱ ዕለታት በየቀኑ እስከ አንድ ሺሕ የሚሆኑ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን