• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

0006

በአ/አ/ ሀገረ ስብከት በመዋቅርና የአሠራር መመሪያ ጥናት ረቂቅ ሰነድ ላይ ለ2 ቀናት ሲካሄድ የቆየውን የመጀመሪያ ዙር የውይይት መርሃ ግብር ተጠናቀቀ

                                                     በሀገረ ስብከቱ አይቲና ዶክሜንቴሽን ክፍል ህዳር 17 እና 18/2006 ዓ.ም የቤተ ክርስቲያኒቱ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፤የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፤የሀገረ ሰብከቱ የዋና ክፍል እና ክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት ለ2 ሙሉ ቀናት ሲካሄድ የቆየው ከሀገረ ስብከት እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት መልካም የሥራ ጅምር የሆነውን የሀገረ ስብከቱ መዋቅራዊና የአሠራር መመሪያ ጥናት ረቂቅ ሰነድ ላይ ለአዘጋጆችና አቅራቢ ባለሞያዎች […]

0014

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የነበርውን የመልካም አስተዳደር እና የፋይናንስ ችግር ሙሉ በሙሉ ይፈታል በተባለው መዋቅርዊ የአሠራር ለውጥ እና አደረጃጀት ላይ ውይይት በመካሄድ ላይ ነው

ቀደም ብለን በድህረ ገፃችን ስናሰራጭ እንደቆየነው ሀገረ ስብከቱ ከሚያዘያ 2005 ዓ.ም ጀምሮ በአሠራር ለውጥ ውስጥ የቆየ ሲሆን በዚህም መነሻነት ሀገረ ስብከቱ በቃለ ዓዋዲው መሠረት በ7 ወረዳ/ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ተዋቅሮ ለ3 ወራት የሚያገለግል ጊዚያዊ ውስጠ ደንብ ከመዘጋጀቱም በላይ ከሀገረ ስብከቱ እስከ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ድረስ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ከዚሁ ጎን ለጎን አዲሱ […]

b003

በአ/ሀ/ስ/የአራዳ ጉለሌ ክ/ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት በወረዳው ስለ ተሠሩ ሥራዎች ሪፖርት አቀረበ

                             ሪፖርት

b003

– ብፁዕ አባታችን አቡነ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት እና የጅማ ሀገረ ስብከተ ሊቀ ጳጳስ

– ክቡር ንቡረ ዕድ አባ ዮሐንስ ገ/ሕይወት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ – ክቡራን የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች

– ክቡራን የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች እና የልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊዎች

ቸሩ አምላካችን እና አባታችን ሕይወታችንን በቸርነቱ ጠብቆ፣ ሥራችንን ባርኮ እና ቀድሶ ለዚህች ሰዓት ስለአደረሰን ክብርና ምስጋና ለስመ አጠራሩ ይሁንልን አሜን::

ማዕረሩ ብዙህ በገባሩኒ ህዳጥ ሰአልዎ እንከ ለበዐለ ከመይወስክ ገባዕተ ለማዕረሩ (ማቴ. 9፡37) መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የመንግሥተ እግዚአብሔርን ወንጌል በሚአስፋፋበት ወቅት በየምኩራቡ በመሄድ የእግዚአብሔርን መንግሥት መልካም ዜና እያበሠረ ሕዝቡን ከበሽታ እና ከደዌ እየፈወሰ ህዝቡ እረኛ እንደሌላቸው በጎች ተጨንቀው እና ተቅበዝብዘው፣ ረዳት አጥተው ባያቸው ጊዜ ራራላቸው እና ከአጠገቡ ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን መከሩ ብዙ ነው የመከሩ ሠራተኞች ግን ጥቂቶች ናቸው የመከሩ ባለቤት ተጨማሪ ሠራተኞችን እንዲልክ ለምኑት በማለት ጥበብ የተሞላበትን መልእክት አስተላልፏል፡፡

የሥራ ጀማሪ ራሱ እግዚአብሔር መሆኑን ወንጌላዊ ቅዱስ ዮሐንስ እንዲህ በማለት ይናገራል “አባቴ እስከ አሁን እየሠራ ነው እኔም ደግሞ እሠራለሁ” (ዮሐ. 5፡17) ዛሬም ቢሆን እግዚአብሔር ሥራውን አላቋረጠም፡፡ እኛም ደግሞ ከእርሱ ልንማር ይገባናል፡፡ (ማቴ. 11፡28) አምላካችን እግዚአብሔር ሰውን የፈጠረው ለሥራ እንደሆነ በቅዱስ መጽሐፍ አስቀድሞ ተናግሯል፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ሰውን ወስዶ እንዲአለማት እና እየተንከባከበ እንዲጠብቃት በኤደን የአትክልት ቦታ አስቀመጠው (ዘፍ. 2፡15) ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ በበኩሉ ስለ ሥራ አስፈላጊነት ሲናገር ሊሠራ የማይወድ አይብላ በማለት ተናግሯል፡፡ (2ተሰ 3፡8) በዚህ ሕገ እግዚአብሔር መሠረት የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዕቅድ አውጥቶ ተገቢውን ሁለገብ የሥራ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡

የክፍለ ከተማ ቤተክህታችን የተመሠረተው ከሐምሌ 24 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ ሲሆን

640

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአዲሱ መዋቅርዊ የአሠራር ለውጥ እና አደረጃጀት ላይ ውይይት ሊካሄድ ነው

አዲሱ የሀገረ ስብከቱ መዋቅራዊ የአሠራር ለውጥና አደረጃጀት እጅግ ከፍትኛ ልምድ ባላቸው የቤተ ክርስቲያኒቷ ልጆች ተዘጋጅቶ ለጥቅምት 2006 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ቀርቦ ከታዬ በኋላ ለሀገረ ስብከቱ ያለው ጠቃሚነት እጅግ የላቀ መሆኑን ስለታመነበት የሚመለከታቸው አካላት ውውይት አድርገውበት በቋሚ ሲኖዶስ እንዲፀድቅ በተወሰነው መሠረት የመጀመሪያው ዙር ውውይት ህዳር 17 እና 18/2006 ለሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎች፤ የክፍል […]

0337

እንኳን ለሊቀ መላእክት ለቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓለ በሰላም አደረሰን አደሳችሁ!

0337

በዚህች ቀን የሰማይ ሰራዊት ሁሉ አለቃቸው መልአከ ምክሩ የምክሩ አበጋዝ ይለዋል የቅድስት ሥላሴ መንጦላእትን የሚከፍትና የሚዘጋ ለፍጥረት ሁሉ የሚማልድ  ታላቁ  መልአክ ቅዱስ ሚካኤል የተሾመበት ቀን ነው። በህዳር ወር በዐሥራ ሁለተኛው ቀን ቤተ ክርስቲያናችን የታላቁ መልአክ የቅዱስ ሚካኤልን በዓለ ሲመት በታላቅ ምቀት ታከብረዋለች፡፡ እንደ ቅዱሳን አባቶቻችን አስተምህሮ ህዳር 12 ቀን ታላቁ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል በኢዮር ባለችው በአራተኛይቷ ከተማ በሚኖሩት ኃይላት እና በአሥሩ ነገደ መላእክት ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት ቀን ነው፡፡እግዚአብሔር ሳጥናኤልን በትዕቢቱ ምክንያት ከሥልጣኑ ገፍፎ ወደ ምድር ሲጥለው ቅዱስ ሚካኤል በእርሱ ቦታ በዐሥሩ ከተማ በመቶውም ነገደ መላእክት ላይ ተሹሟል፡፡(ይህን ሁለተኛውን ሹመት ያገኘው በሚያዚያ 2 እንደሆነ አክሲማሮስ በሚባለው የቤተክርስቲያናችን መጽሐፍ ላይ ሰፍሮ አናገኛለን፡፡)
የቅዱስ ሚካኤል ሹመት በነገደ መላእክት ላይ ብቻ ግን አይደለም ነገር ግን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሆኑት ላይም ጭምር ነው ፡፡ ይህም እንደሆነ እንድንረዳ በብሉይ ኪዳን የእግዚአብሔር ሕዝብ የተባለውን እስራኤል ዘሥጋን ሲራዳና ሲጠብቅ እንደነበረ ተጽፎልን እናገኛለን፡፡ ለምሳሌ መጽሐፍ ቅዱስ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ለኢያሱ በኢያሪኮ ምድረ በዳ እንደተገለጠለት “… ዐይኑን አንሥቶ ተመለከተ እነሆም የተመዘዘ ሰይፍ የያዘ ሰው በፊቱ ቆመ፤ ኢያሱም ወደ እርሱ ቀርቦከእኛ ወገን ወይስ ከጠላቶቻችን ወገን ነህ? አለው፡፡ እርሱምእኔ የእግዚአብሔር ሠራዊት አለቃ ሆኜ አሁንም ወደ አንተ መጥቼአለሁ” (ኢያ.513) ይለናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንዲህ አለበሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱም ዘንዶውን ተዋጉት፥ ዘንዶውም አልቻላቸውም፥ ከዚያም በኋላ በሰማይ ቦታ አልተገኘለትም። ራእ 127 ነብዩ ዳንኤልም እንዲህ አለበዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣልዳን ፲፪፥፩።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ቅዱሳን መላእክት እኛን እንደሚጠብቁና እንደሚራዱ እንዲሁም ስለእኛ በፊቱ አንደሚቆሙ ሲያስተምረንከእነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን ስንኳ እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፤ መላእክቶቻቸው በሰማያት ሁል ጊዜ በሰማይ ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁ” (ማቴ.1810) ብሎናል፡፡ እኛን ይጠብቁ ዘንድ የተሰጡን ቅዱሳን መላእክት ስለእኛ እንዲህ የሚቆረቆሩና ስለመዳናችን የሚተጉ ከሆነ በቅድስናው ልቆ የመላእክት አለቃ ሆኖ የተሾመው ቅዱስ ሚካኤል እንዴት ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ይበልጥ አይቆም? (ሉቃ.136-9) እንዴትስ በተሰጠው ሥልጣንና ኃይል አይረዳን? (መዝ.337) እርሱስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመውመባሉም እኛን በጸሎቱና በተራዳኢነቱ የጽድቅ ሕይወታችንን በሚገባ እንድናከናውን እንደሚራዳን የሚያሳይ ኃይለ ቃል ነው፡፡

በመጽሐፈ ዳንኤልእነሆም፥ ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ” (ዳን 1013) የሚለውን ቃል ስናነብ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በእግዚአብሔር ቀና መንገድ ላይ የሚጓዙትን፤ በእምነት የጸኑትን ሊረዳ እንደሚፋጠን እንገነዘባለን።

በመጽሐፈ ዘካሪያስም እንዲህ የሚል ቃል ተጽፎ እናገኛለንየእግዚአብሔርም መልአክ መልሶ። አቤቱ፥ የሠራዊት ጌታ ሆይ፥ እነዚህ ሰባ ዓመት የተቈጣሃቸውን ኢየሩሳሌምንና የይሁዳን ከተሞች የማትምራቸው እስከ መቼ ነው? አለ። ” (ዘካ 112) መልአኩ ይህንን ልመና በእግዚአብሔር ፊት ያቀረበው እስራኤላውያን በበደላቸው ምክንያት ለግዞት ተላልፈው በተሰጡበት ዘመን መሆኑ ልመናውን ልዩ ያደርገዋል። በበደላቸው ጊዜ፤ በደከሙና በግዞት በወደቁ ጊዜ መልአኩ ስለእነርሱ በእግዚአብሔር ፊት እንደቆመ ማስተዋል የመላእክትን ተራድኦ ያመላክታል። እግዚአብሔር አምላክም ይህንን በሐዘን የቀረበ የመልአኩን ልመና ተቀብሎ ለእስራኤላውያን የምሕረት ፊቱን እንደመለሰላቸው እናነባለንስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ወደ ኢየሩሳሌም በምሕረት ተመልሻለሁ፤ ቤቴ ይሠራባታል፤ . . . ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር።” (ዘካ 117)

0336

የኢትዮጵያ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅደስ አቡነ ማትያስ በአሜሪካ ሐዋርያዊ ጉዞ አደረጉ

ቅደስነታቸው በአሜሪካ ባደረጉት ሐዋርያዊ ጉዞ ከበርካታ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያት ጋር ውይይት አካሒደዋል ፡፡ ብፁዕ ወቅደስ አቡነ ማትያስ ቀዲማዊ ፓትርያርክ በውይይቱ ወቅት እንደተናገሩት በዓለም ላይ የፖለቲካና የሃይማኖት ልዩነት ተፈጥሮአዊ በመሆኑ በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሁሉም በጋራ እንዲሠሩ ጠይቀዋል ፡፡ ቅዱስ ፓትርያርኩና ተከታዮቻቸው በአሜሪካ በተለያዩ ክፍላተ ሀገር በመዘዋወር ስለ አንድነት፣ ሰላምና ትብብር ከኢትዮጵያውያኑ ጋር ውይይት አድርገዋል ፡፡ በአንድ […]

2021

የ2006 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዐተ ጉባኤ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቀቀ

ጉባኤው ከጥቅምት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ ላለፉት 10 ቀናት ተወያይቶ ያሳለፋቸውን ውሳኔዎች አስመልክቶ ጥቅምት21/2006 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በተገኙበት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡ የመግለጫውን ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይቀርባል፡፡ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን […]

32ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ ተጠናቀቀ

ለተጨማሪ ንባብ እዚህ ላይ ይጫኑ (ሙሉ የአቋም መግለጫና ቃለ ገባኤ) {flike}{plusone}

0004

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአራዳ ጉለሌ ክፍለ ከተማ ጽ/ቤት በሥሩ ካሉ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በልማት ዙሪያ ውይይት አካሄደ

መስከረም 29/1/06 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ሥር ከሚገኙ አስተዳዳሪዎች፤ ፀሐፊዎች፤ቁጥጥሮች፤ሒሳብ ሹሞችና ሰባክያነ ወንጌል ጋራ ስብሰባ የተካሄደ ሲሆን በዚሁ ስብሰባ ላይ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትያርክ ረዳት ሊቀ ጳጳስ እና የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል፡፡ ሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ ስለ ክፍለ ከተማው አስመልክተው ሰፊ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በልማትና በመልካም አስተዳደር እንዲሁም […]

h002

32ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በመካሄድ ላይ ነው፡፡

32ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ መደበኛ ስብሰባ ጥቅምት 4 ቀን 2006 ዓም. በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተጀምሯል፡፡ በመደበኛ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤው ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ የመምሪያ ሓላፊዎች፤ የየሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጆች፤ ሰንበት […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን