• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

0011

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች የ3 ቀን የግንዛቤ ማስጨባጫ ሥልጠና ተሰጠ

               በመ/ር ዘሩ እና በመ/ር ኃይሉ “ክፉውን ነገር ተጸየፉት ከበጎ ነገር ጋር ተባበሩ”ሮሜ 12÷9 መልካም አስተዳደር ለዘላቂና ሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን እድገት በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ሥልጠና የተጀመረው ሐምሌ 9/2005 ዓ.ም ጀምሮ ሲሆን ሥልጠናው እየተካሄደው ያለውም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የስብከተ ወንገል አዳራሽ ነው፡፡ በዚሁ በዓይነቱ ልዩ የሆነው ሥልጠና ተካፋይ የሆኑ ሥራ ኃላፊዎች፡- 1. የሀገረ ሰብከት […]

md1

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት ኃላፊዎች ከብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአ/አ/ሀ/ስ/የቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀጳጳስና ከአ/አ/ሀ/ስ/ዋና ስራ አስከያጅ ጋራ የትውውቅ መርሃ ግብር ተካሄደ

                                   በመ/ር ዘሩ እና በመ/ር ኃይሉ ሰኔ 14/2005 ዓ.ም ከጠዋቱ 2.30 ጀምሮ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት መሰብሰቢያ አዳራሽ የትውውቅ መርሃ ግብሩ የተካሄደ ሲሆን በዚሁ ዕለት አዲሱ አስከያጅ መጋቤ ሐዲስ ይልማ ቸርነት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በአ/አ/ሀ/ስ/የቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት ሊቀጳጳስ አማካኝነት /ጋባዥነት ራሳቸውን እንዲያስተዋውቁ በተፈቀደላቸው መሠረት በአጭሩ ከጀመሪያ ጀምሮ ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አሰከያጅነት እሰከ […]

0001

የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ ተጠናቀቀ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ላይ ከበዐለ ትንሣኤ በኋላ በሃያ አምስተኛው ቀን የቅዱስ ሲኖዳስ ጉባኤ እንዲካሔድ በተደነገገው ቀኖና ክርስቲያን መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ከግንቦት 21-30 ቀን 2005 ዓ.ም ተካሒዷል፡፡ ይህ ጉባኤ የርክብ ካህናት ጉባኤ ተብሎ የሚታወቅ ሲሆን ከላይ በተጠቀሰው ቀኖና […]

009

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ መልዕክት አስተላለፉ

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በእንተ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

009
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

  1.   በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ፤
  2. ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፤
  3.   የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችኹ፤
  4.   በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችኹ፤
  5. እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ኾናችኁ በማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤

በትንሣኤው ትንሣኤያችንን ያበሠረን ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳ ለ፳፻፭ ዓ.ም በዓለ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችኹ፡፡

‹‹እስመ ሐደሰ ለነ ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት ንቅረብ እንከ በልበ ጽድቅ›› ‹‹የሕይወትና የእውነት መንገድን አድሶልናልና ከእንግዲህ በቅን ልቡና ወደ እርሱ እንቅረብ›› (ዕብ. 10÷19) የሰው ልጅ ለማያረጅና ለማያልፍ ሕይወት የታደለ፣ በእግዚአብሔር አምሳልና አርአያ የተፈጠረ፣ እጅግ ክቡርና ታላቅ ፍጥረት እንደነበረ ቅዱሳት መጻሕፍት ይመሰክራሉ፤ በምድር በሚገኙ ፍጥረታት ሁሉ ላይ ያለው የበላይነት ሥልጣንም ይህን ያረጋግጣል፡፡

{flike}{plusone}

007

ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የሰሜን እና የምሥራቅ አዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ መልዕክት አስተላለፉ

የብፁዕ አቡነ ዳንኤል የሰሜን እና የምሥራቅ አዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልዕክት አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነስቷል፡፡ 1ኛ ቆሮ 15.20 ብፁዕ አቡነ ዳንኤል የሰሜን እና የምስራቅ አዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለክብርና በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ እንዲኖር የተፈጠረው የሰው ልጅ በአዳምና በሔዋን የእግ/ርን ትዕዛዝ መጣስ የተነሳ ከሕይወት ወደ ሞት፣ ከክብር ወደ […]

4

የሰሜን አዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ የትንሳኤ በዓልን አስመልክቶ መልዕክት አስተላለፉ

“ቃለ እግዚአብሔር ተንሥአ ወሥጋሁኒ ኢማሰነ” የእግዚአብሔር ቃል ተነሣ ሥጋውም ጥፋት አላገኘውም፤ መበስበስም አልገጠመውም ሥ.ቅዳሴ 256 መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ የሰሜን አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስከያጅ መልዕክት ከዘመናት ቁጥር ልኬት በአፍአ የሚኖር ዘመን እና ዘመናት የማይወስኑት መጀመሪያ በሌለው ቅድምና የነበረ ቃል፣ በእግዚአብሔር ዘንድ የነበረ፤ እርሱ እግዚአብሔር፤ አካላዊ ቃል በተለየ አካሉ ከድንግል ማርያም ሥጋን ተዋሃደ፤ […]

004

ዕለታተ ሰሙነ ሕማማት

ሰሙነ ሕማማት ምንድን ነው? ከዕለተ ሆሣዕና ሰርክ እስከ ትንሣኤ ሌሊት ያለውን ጊዜ ወይም ቀናት የሚያመለክት ነው፡፡ ሐመ ማለት ታመመ ማለት ሲሆን ይህም የሰውን ዘር ሁሉ ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ ለማውጣት ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ የተቀበላቸውን ጸዋትወ መከራዎች የሚያሳስብ ነው፡፡ ዕለታቱ የዓመተ ኩነኔ ወይም የዓመተ ፍዳ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ውለታ እያሰቡ እጅግ የሚያዝኑበት፣ የሚያለቅሱበት፣ የሚሰግዱበት […]

የሰሙነ ሕማማት ሃይማኖታዊና ቱፊታዊ ክንዋኔዎች

በዐቢይ ጾም ከሰርክ ሆሳዕና ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡ በእነዚህ ዕለታት ውስጥ የተለያዩ ትውፊታዊ እና ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች አሉ፡፡ ከነዚህ ክንዋኖዎች ውስጥ አለመሳሳም፣ አክፍሎት፣ ቄጤማ ማሰር፣ ጥብጠባ፣ ጉልባን እና ሕፅበተ እግር ይገኙበታል፡፡ ስለእነዚህ ክንዋኔዎች በቅድስት ቤተ ክስቲያን ስላለው ትውፊታዊ አፈፃፀም መዛግብት አገላብጠን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡

{flike}{plusone}

002

በዓለ ሆሳዕና እና ታሪኩ

            እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና በሰላም አደረሳችሁ!! የሆሳዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩስአሌም ሲገባ የሚቀድሙት እና የሚከተሉት ህዝብ በተለይም አእሩግ እና ህጻናት “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሳዕና በአርያም “ በማለት ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው። ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ […]

በሃይማኖት ሽፋን ቅ/ኤልያስ መጥቷል ብለው በኤልያስ ስም ሲነግዱ የነበሩ ግለሰቦች ንፁሀን ዜጎችን ሲያስደበድቡና ሁከት ሲፈጥሩ እጅ ከፍንጅ ተይዘው ታሰሩ

ቀደም ሲል በዚህ ርዕሰ ጉዳይ ላይ በተለያዩ የቤተክርስቲያኒቷ አገልጋዮች የተፃፉትን ጽሑፎች በአህጉረ ስብከታችን ዌብ ሳይት ስናስነብብ መቆየታችን አይዘነጋም፡፡ ምንም እንኳን ጉዳዩ ዘግይቶ በተለያዩ ሚዲያዎች መሰራጨት የጀመረ ቢሆንም ቀደም ሲል ከሁለት ዓመታት በፊት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጀርባ በተለምዶ ቆሎ ሰፈር ተብሎ በሚጠራው መንደር ቤተክርስቲያኑንና ህብረተሰቡን ሲረብሹ የቆዩ ሲሆን የካቴድራሉ ጽ/ቤት ጉዳዩን እየባሰ ሲሄድ በመስከረም […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት