• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

00023

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የኢየሩሳሌም ድርጅት የ50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮቤልዩ በዓሉን በታላቅ ድምቀት አከበረ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የቀድሞው የኢፊድሪ ፕሮዝዳንት ዶ/ር ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና የማኀበሩ አባላት በተገኙበት ግንቦት 16 ቀን 2006 ዓ.ም ቦሌ በሚገኘው የማህበሩ ማዕከል የ50ኛ ዓመት የወርቅ ኢዮበልዩ የምሥረታ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፡፡ የድርጅቱን የ50 ዓመት […]

a004

የቀድሞው የኦሮሚያ ክልላዊ ፕሮዝዳንት የክቡር አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ የ80 ቀን መታሰቢያ በዓል ተከበረ፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ክቡር አቶ ሙክታር ከድር የኦሮሚያ ክልላዊ ፕሮዝዳንት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሚኒስትሮች፣ የክቡር አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ የቅርብ ዘመዶች እና ወዳጆች በተገኙበት ግንቦት 16 ቀን 2006 ዓ.ም በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የአቶ ዓለማየሁ አቶምሳ የ80 ቀን መታሰቢያ በጸሎት […]

0990

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ምሩቃን አንድነት ጉባኤ የ3ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን በታላቅ ድምቀት አከበረ

ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፤ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንገዶች ፤ተመራቂ ደቀ መዛሙርት፤ የኮሌጁ መምህራንና ደቀ መዛሙርት በተገኙበት ግንቦት 10/2006 ዓ.ም በጠቀላይ ቤ/ክ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ የአንድነት ጉባኤ የምስረታ በዓሉ በታላቅ ድምቀት ተከብሯል፡፡በዓሉ በተከበረበት ወቅት ከዝግጂት ክፍሉ የቀረበውን ጠቅላላ ሪፖረት እንደሚከተለው አቅረበነዋል፡፡    “ወአዲ እብለህክሙ ለእመ ኃብሩ ክልኤቱ አዉ ሠለስቱ እምኔክሙ በውስተ ምድር በእንተ ኩሉ ግብር ዘሰዓሉ ይትገበር ሎሙ […]

0051

የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጀመረ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜንብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትሞትን በሞቱ ድል አድርጎ፣ ሙስና መቃብርን አጥፍቶ፣ በኃይለ መለኮቱ ከሙታን ተለይቶ የተነሣው ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁላችንንም በልዩ አጠራሩ ጠርቶ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት በሚካሄደው በዚህ ክርስቶሳዊና ሐዋርያዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ ስለሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፡፡ “ወንሩጽ በትዕግሥት ኀበ ዘጽኑሕ ለነ […]

0908

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2006 ዓ.ም. የትንሣኤ በዓልን አስመልክቶው ቃለ ምዕዳን አስተላለፉ

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትበእንተ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን•    በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣•    ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምኖሩ፣•    የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፣ •    በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ፣•    እንዲሁም የሕግ […]

e001

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ረዳት እና የጅማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ መልእክት

                                    በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊትና ሥርዓት መሠረት የያዝነው አርባ ጾም ከሰባቱ አጽዋማት አንዱ ሲሆን ይህም ጾም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተጠመቀ በኋላ የጾመው ነው፡፡ ይህም ጾመ  አርባ ወይም ዐቢይ ጾም በኦርቶዶክስ ተወሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ክብር የሚሰጠው […]

004

ዕለታተ ሰሙነ ሕማማት

ሰሙነ ሕማማት ምንድን ነው? ከዕለተ ሆሣዕና ሰርክ እስከ ትንሣኤ ሌሊት ያለውን ጊዜ ወይም ቀናት የሚያመለክት ነው፡፡ ሐመ ማለት ታመመ ማለት ሲሆን ይህም የሰውን ዘር ሁሉ ከዲያብሎስ ባርነት ነፃ ለማውጣት ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ የተቀበላቸውን ጸዋትወ መከራዎች የሚያሳስብ ነው፡፡ ዕለታቱ የዓመተ ኩነኔ ወይም የዓመተ ፍዳ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ክርስቲያኖች የክርስቶስን ውለታ እያሰቡ እጅግ የሚያዝኑበት፣ የሚያለቅሱበት፣ የሚሰግዱበት […]

pp002

በአዲስ አበባ ገዳማት እና አድባራት ልዩ የስብከተ ወንጌል የአንድነት ጉባኤ መርሐ ግብር ተጀመረ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልዕኮ ዋና ክፍል አስተባባሪነት የተጀመረው የአድባራት እና ገዳማት የአንድነት ጉባዔ የተጀመረው የካቲት 11 ቀን 2006 ዓ.ም በቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ሲሆን ጉባዔው እስከ ሰኔ 30 ቀን 2006 ዓ.ም ድረስ የአንደኛው ዙር ጉባዔ ይካሄዳል፡፡ የአንድነት ጉባዔው በምድብ እየተመደበ የሚካሄድ ሲሆን አንድ ምድብ ከሶስት አድባራት እስከ አስር […]

0094

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ የሃይማኖት መሪዎች ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን እና የድኅነትን አስከፊነት አስመልክተው ለግማሽ ቀን የቆየ የጋራ ምክክር አደረጉ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የሃይማኖቶች ጉባኤ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን የምክክሩን ጉባኤ አስመልክተው የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት ወቅት የሚከተለውን መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን  ከሩቅም ከቅርብም አሰባስቦ እርሱ የሚከብርበትን ሥራ እንድንሠራ እንደዚህ ተሰብስበን ስለ ሀገራችን ችግር እንድንወያይ ስለፈቀደልን የተመሰገነ ይሁን፡፡ ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን እና የልመናን አስከፊነት ለማስወገድ የአዲስ አበባ […]

640

የአዲስ ኣበባ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ምክንያቶች ከሥራ ገበታቸው ታግድው የቆዩትን ሠራተኞች ወደ መደበኛ ሥራቸው እንዲመለሱ አደረገ

በአሁኑ ወቅት ሀገረ ስብከቱ መልካም አስተዳደር ለማስፈን እያደረገው ካለው መልካም የሥራ እንቅስቃሴ መካከል አንዱ  በእንዳንድ ገደማትና አድባራት ያለአግባብ የሚታገዱትና የሚባረሩትን ሠራተኞች ትክክለኛ የሆነ ውሳኔና መፍትሄ መስጠት ነው፡፡በአሁኑ ሰዓት ገዳማትና አድባራት ከአቅማቸው በላይ ሠራተኞች በመያዛቸው የተነሳ ለጊዜው  ቅጥር እንዲቆም የተደረገ ሲሆን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ግን ለሥራ መደቡ የሚያስፈልገውን መስፈርት ወጥቶለት በህጉና በሥርአቱ መሰረት ቅጥርም ሆነ እድገት […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት