ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን(ሥርዓቴን ጠብቁ)November 30, 2015 በላዕከ ወንጌል በእደ ማርያም ይትባረክ (ቀሲስ) የአ/አ/ሀ/ስ/የስብከተ ወንጌል ትምህርት ሥርጭት ኃላፊ “ሥርዓቴን ጠብቁ”ዘሌዋ. 19፡19 ሥርዓት፡- ቃሉ ግዕዝ ነው፡፡ ሠርዐ፡ ሠራ ከሚለው ግሥ የወጣ ሲሆን ሥርዓት ማለት ሕግ፣ ደንብ ማለት ነው፡፡ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ማለት የቤተክርስቲያን ሕግ የቤተክርስቲያን ደንብ ማለት ነው፡፡ ከላይ በጽሑፉ መነሻ እንደተጠቀሰው ሥርዓት መጠበቅ እንዳለብን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አዟል፡፡ በቤተክርስቲያናችን የሚፈጸሙ ብዙ ሥርዓቶች አሉ፡፡ ቤተክርስቲያን ሄደን ገና ከውጭው በር ላይ ስንደርስ ስመ ሥላሴን እየጠራን በትእምርተ መስቀል እያማተብን “ሰላም ለኪ አምሳለ ኢየሩሳሌም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን” (የኢየሩሳሌም አምሳል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም ላንቺ ይሁን) እያልን ሦስት ጊዜ ለቤተክርስቲያን ሰላምታ እንሰጣለን፡፡ ለቤተክርስቲያን ሰላምታ መስጠት እንደሚገባ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፏል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ለቤተክርስቲያን ሰላምታ ከሰጠ በኋላ ወደ አንጾኪያ ወረደ” የሐዋ. ሥራ 18፡22 ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ ከገባን በኋላ ወደ ውስጥ እንገባል ስንገባም ወንዶች በወንዶች በር፣ ሴቶች በሴቶች በር ካህናትም በካህናት በር ይገባሉ፡፡ የሚሳለሙትም ሁሉም በየበራቸው ነው፡ ውስጥ ከገባን በኋላ ወንዶች በወንዶች መቆሚያ ሴቶች በሴቶች መቆሚያ ይቆማሉ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ሴቶች ቤተ ክርስቲያን ሲገቡ ራሳቸውን መከናነብ አለባቸው፡፡ 1ኛ ቆሮ 11፡5 በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ የሚፈጸሙ ብዙ ሥርዓቶች አሉበጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ከሚፈጸሙት ሥርዓቶች ጥቂቶቹ እንደሚከተለው ተገልጸዋል፡፡በቅዳሴ ጊዜ ለቅዳሴ ከተሰየሙት ልዑካን በስተቀር መውጣት፣ መግባት፣ መዘዋወር አይፈቀድም፡፡ የተቻለው ተሰጥዎውን መቀበል ያልተቻለው በጽሙና ሆኖ ጸሎተ ቅዳሴውን መከታተል ያስፈልጋል፡፡ በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ “ስግዱ ለእግዚአብሔር በፍርሃት” (ለእግዚአብሔር በፍርሃት ስገዱ) ይላል ሁላችንም በግምባራችን ተደፍተን እንሰግዳለን ቄሱ ፍትሐት ዘወልድ ይደግማሉ በመቀጠል ዲያቆኑ በእንተ ቅድሳት ይደግማል፡፡ ከዚያም ዲያቆኑ “ተንሥኡ ለጸሎት” (ለጸሎት ተነሡ) ይላል ሰግደን የነበርነው እንነሳለን ይህ ምሳሌ አለው፡፡ ስገዱ ሲለን መስገዳችን በኃጢአት የመውደቃችን ምሳሌ ነው ተነሡ ሲለን መነሣታችን ደግሞ Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png 0 0 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-30 14:36:292023-11-09 10:25:33ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን(ሥርዓቴን ጠብቁ)
የአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት ለአድባራትና ገዳማት የሒሳብ ሠራተኞች ሁለተኛ ዙር የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና መስጠት ጀመረNovember 25, 2015በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሒሳብና በጀት ዋና ክፍል እየተዘጋጀ ሲሰጥ የቆየው የአድባራትና ገዳማት የሒሳብ ሠራተኞች የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ለሁለተኛ ዙር ተጠናክሮና ተሻሽሎ ለሠልጣኝ ሠራተኞች እየተሰጠ መሆኑ ታወቀ፡፡የሁለተኛው ዙር ሰልጣኝ ሠራተኞች ቁጥራቸው ሰላሳ የሚደርስ ሲሆን ሦስቱ ሠልጣኞች የሀገረ ስበከቱ ሠራተኞች ናቸው፡፡ ሠልጣኝ ሠራተኞች በሥልጠናው የሚቆዩት ለአንድ ወር ብቻ ሲሆን የመጀመሪያው ዙር […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/0856.jpg 425 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-25 14:40:592023-11-09 10:25:33የአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት ለአድባራትና ገዳማት የሒሳብ ሠራተኞች ሁለተኛ ዙር የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና መስጠት ጀመረ
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት በሥራ እንቅስቃሴያቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አድባራትና ገዳማት የማበረታቻ ሽልማት አበርከተላቸውNovember 25, 2015 በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስና የሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት በልማት፣በመልካም አስተዳዳርና በፐርሰንት ክፍያ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አድባራትና ገዳማት የዋንጫ ሽልማት አበርክቶላቸዋል፡፡ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በአደስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሥር ካሉት ሰባት ክፍላተ ከተሞች አንዱ ሲሆን በምዕራብ አዲስ አበባ፣ የኦሮምያ ክልል ልዩ ዞን የቡራዮ አስተዳደርና የሰበታ አስተዳደር የሚያዋስነው የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ነው፡፡የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሃያ ሰባት አድባራትና ገዳማት የሚገኙበት ነው፡፡ የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቱ በሰለጠነ የሰው ኃይል የተገነባ መሆኑን በስብሰባው ወቅት ከቀረበው ሪፖርት ለመረዳት ችለናል ÷ በሳምንት አንድ ቀን የሥራና የሠራተኛ ግምገማ እንደሚደረግ ሪፖርቱ አክሎ አብራርቷል ÷ በሪፖርቱ ላይ እንደተዘረዘረው ያለ በቂ ምክንያት ከሥራ የታገዱ ሠራተኞችም ወደሥራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡በዝቅተኛና ያለጨረታ የተከራዩ የአብያተ ክርስቲያናት ቦታዎችም የኪራይ ውላቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡ሰላምን የሚአደፈርሱና ሁከት የሚፈጥሩ አንድ አንድ ወገኖች ከመጥፎ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ የምክር አገልግሎት እየተሰጣቸው ነው፡፡ የምርጫ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ የሰበካ ጉባኤ አባላት በአዲስ ተመራጭ እንዲተኩ ተደርጓል፡፡ የፐርሰንት ክፍያ ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ዕውቅና ያልተሰጣቸው ሰባክያን የወንጌል አገልግሎት እንዳይሰጡ የተደረገ ሲሆን ሕጋዊ የሆኑ ሰባክያን ግን የወንጌል ትምህርት እንዲሰጡ ሁኔታዎች ተመቻችተዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን ተተኪ ትውልድ ለማፍራት ወጣቶች 30 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ በሰንበት ት/ቤቱ እየተማሩ እንዲአድጉ በትጋት እየተሠራ ነው፡፡ከዚህም ጐን የቅርስ ጥበቃ የልዩ ልዩ ልማት እንቅስቃሴ፣እየተከናወነ ነው፡፡ በ2008 ዓ.ም የበጀት ዓመት በሩብ ዓመት ውስጥ ብር4,000,000 አራት ሚሊዮን ብር የፐርሰንት ክፍያ ገቢ ተደርጓል ÷ በክፍለ ከተማው ያገጣሙ ችግሮችን በተመለከተ የኮምፒውተር ጸሐፊ፣ መዝገብ ቤት፣ ተላላኪ አለመመደቡ፣ የትራንስፖርትና የቢሮ ቁሳቁስ አለመሟላት፣ በአንድ አንድ አድባራትና ገዳማት የሚገኙ የሰበካ ጉባኤ ሊቃነ መናብርት በዕንቢተኝነት የደመወዝ ፊርማ አለመፈረም፣ አንድ አንድ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የቃለ ዓዋዲውን ሕግ ጠብቀው አለመሥራት አንድ አንድ ማህበራት በማይመለከታቸው ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የአስተዳደር ሥርዓቱን ለማወክ የሚደረገው ሴራ ዋና ዋና ችግሮች Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/0866.jpg 425 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-25 14:38:122023-11-09 10:25:33የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት በሥራ እንቅስቃሴያቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አድባራትና ገዳማት የማበረታቻ ሽልማት አበርከተላቸው
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘት ጠንክሮ እየሠራ መሆኑ ተገለጸNovember 19, 2015 በመ/ር ሣህሉ አድማሱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘትና የተሻለ የሥራ መነቃቃትን ለመፍጠር በማሰብ ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ጀምሮ እስከ አድባራትና ገዳማት የደረሰ የሠራተኛ ዝውውር ተግባር እያከናወነ መሆኑን ተገልጿል፡፡ ሀገረ ስብከቱ ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘት ባለው ቁርጥ አቋም መሠረት ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ከአንዱ የሥራ ክፍል ወደ ሌላው ሥራ ክፍልና ወደ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/640.jpg 480 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-19 13:33:252023-11-09 10:25:33የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘት ጠንክሮ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባስመዘገበው የዕንግዳ አቀባበል የሥራ ጥራት ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የማበረታቻ ምስጋና ደብዳቤ ተቀበለNovember 19, 2015በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በ2008 ዓ.ም የተከበረውንና በዩኒስኮ የቅርስ መዝገብ የተመዘገበውን የመስቀል ደመራ በዓል አስመልክቶ የጉብኝት ተግባር ለማከናወን ወደ ሀገራችን በዕንግድነት የመጡት የአሌክሳንደርያ ፖፕና የመንበረ ማርቆስ ፓትርያርክ የሆኑት ብፁዕ ወቅዱስ ታዎድሮስ ሁለተኛ፣ በተጨማሪም ቅዱስነታቸውን አጅበው የመጡት ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት፣ የልዑካን ቡድን ባደረጉት ሀገር አቀፍ ጉብኝት ላይ ሀገረ ስብከቱ ለጉብኝቱ መሳካት […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/0002001.jpg 640 472 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-19 09:50:262023-11-09 10:25:33የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባስመዘገበው የዕንግዳ አቀባበል የሥራ ጥራት ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የማበረታቻ ምስጋና ደብዳቤ ተቀበለ
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በአዲግራት አድባራትና ገዳማት ሲያከናውኑ የቆዩት የአምስት ተከታታይ ቀናት ሐዋርያዊ ጉብኝት ተጠናቀቀ!!November 14, 2015ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ከሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ፣ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች፣ ከሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎችና ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪች ጋር በመሆን ከጥቅምት 25 ቀን እስከ ጥቅምት 29 […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/0082.jpg 425 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-14 12:34:032023-11-09 10:25:33ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በአዲግራት አድባራትና ገዳማት ሲያከናውኑ የቆዩት የአምስት ተከታታይ ቀናት ሐዋርያዊ ጉብኝት ተጠናቀቀ!!
ቅዱስ ፓትርያርኩ ተወልደው ያደጉበትን አካባቢ እና የሐውዜን ከተማን ተዛውረው ጎበኙNovember 9, 2015ቅዱስነታቸው ክርስትና የተነሱበት ደብር የምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት ጉብኝታቸው ሊጠናቀቀ አምስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት ሐዋርያዊ ጉብኝት የተወለዱበትን፣ የተማሩበትን እና በደርግ ዘመነ መንግሥት ከ2,500 በላይ ወገኖችና ከ20,000.00 በላይ እንስሳት በቦንብ ተደብድበው መሥዋዕት የሆኑበትን የሐውዜን ከተማን ተዘዋውረው ተመልክተዋል አባታዊ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/t0011.jpg 480 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-09 12:48:472023-11-09 10:25:33ቅዱስ ፓትርያርኩ ተወልደው ያደጉበትን አካባቢ እና የሐውዜን ከተማን ተዛውረው ጎበኙ
ቅዱስ ፓትርያርክ የአዲግራት ዩኒቨርስቲን ጎበኙNovember 8, 2015የአዲግራት ዩኒቨርስቲ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል ብፁዕ ወቅዱ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነጳጳሳት ዘኢትዩጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት የጉበኝታቸው አንዱ አካል የሆነውን የአዲግራት ዩኒቨርስቲን ጥቅምት 27 ቀን 2008 ዓ.ም ምሽት ላይ ጎበኝተዋል፡፡የዩኒቨርስቲውን አጠቃላይ ይዞታ ፣የማሪዎችን ዶርምተርና የመመገቢያ ቦታዎችን በመኪና በመዘዋወር የተመለከቱት ቅዱስነታቸው ዩኒቨርስቲ የሚጠቀምበትን የዘመናዊ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል እና ማዕከሉ የሚጠውን […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/t009.jpg 480 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-08 08:16:562023-11-09 10:25:33ቅዱስ ፓትርያርክ የአዲግራት ዩኒቨርስቲን ጎበኙ
የአዲግራት ደብረ መድኃኔት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ተከበረNovember 7, 2015ቅዱስ ፓትርያርኩ በደብሩ ተገኝተው አባታዊ ምክር ሲሰጡ በአዲግራት ከተማ በምሥራቃዊ ዞን ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የአዲግራት ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ ተባርኮ የተመረቀ ሲሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ ይህ ሕንፃ ከተራ ቤትነት ወደ ተቀደሰ ቤተ ክርስቲያንነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ቀኖና መሠረት ተለውጧል፡፡ስለሆነም የአከባቢው ህዝበ ክርስቲያን በገንዘቡ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/t001.jpg 480 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-07 17:10:432023-11-09 10:25:33የአዲግራት ደብረ መድኃኔት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ተከበረ
ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር ያለን የሃይማኖት ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ለሀገር ልማት በጋራ መሥራት እንደሚገባ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አሳሰቡNovember 7, 2015ብፁዕ አቡነ ተሥፋ ሥላሴ የወርቅ ፅዋ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ሲያበረክቱ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቀ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የምሥራቅ ትግራይ ዞን ሐዋሪያዊ ጉዞን በማስመልከት የትግራይ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ተስፋ ሥላሴ፤ካህናት፣ ምዕመናንና በካቶሊክ ቤተክርስቲያን የሚማሩ ተማሪዎች ከአዲግራት ከተማ 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ አቀባበል አድረገውላቸዋል፡፡የአዲግራት ከተማ ሕዝበ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/t006.jpg 480 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2015-11-07 09:37:132023-11-09 10:25:33ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር ያለን የሃይማኖት ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ለሀገር ልማት በጋራ መሥራት እንደሚገባ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አሳሰቡ
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን(ሥርዓቴን ጠብቁ)
በላዕከ ወንጌል በእደ ማርያም ይትባረክ (ቀሲስ) የአ/አ/ሀ/ስ/የስብከተ ወንጌል ትምህርት ሥርጭት ኃላፊ
“ሥርዓቴን ጠብቁ”
ዘሌዋ. 19፡19
ሥርዓት፡- ቃሉ ግዕዝ ነው፡፡ ሠርዐ፡ ሠራ ከሚለው ግሥ የወጣ ሲሆን ሥርዓት ማለት ሕግ፣ ደንብ ማለት ነው፡፡ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ማለት የቤተክርስቲያን ሕግ የቤተክርስቲያን ደንብ ማለት ነው፡፡ ከላይ በጽሑፉ መነሻ እንደተጠቀሰው ሥርዓት መጠበቅ እንዳለብን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አዟል፡፡
በቤተክርስቲያናችን የሚፈጸሙ ብዙ ሥርዓቶች አሉ፡፡ ቤተክርስቲያን ሄደን ገና ከውጭው በር ላይ ስንደርስ ስመ ሥላሴን እየጠራን በትእምርተ መስቀል እያማተብን “ሰላም ለኪ አምሳለ ኢየሩሳሌም ቅድስት ቤተ ክርስቲያን” (የኢየሩሳሌም አምሳል ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላም ላንቺ ይሁን) እያልን ሦስት ጊዜ ለቤተክርስቲያን ሰላምታ እንሰጣለን፡፡
ለቤተክርስቲያን ሰላምታ መስጠት እንደሚገባ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጽፏል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ለቤተክርስቲያን ሰላምታ ከሰጠ በኋላ ወደ አንጾኪያ ወረደ” የሐዋ. ሥራ 18፡22
ቤተ ክርስቲያን ግቢ ውስጥ ከገባን በኋላ ወደ ውስጥ እንገባል ስንገባም ወንዶች በወንዶች በር፣ ሴቶች በሴቶች በር ካህናትም በካህናት በር ይገባሉ፡፡ የሚሳለሙትም ሁሉም በየበራቸው ነው፡ ውስጥ ከገባን በኋላ ወንዶች በወንዶች መቆሚያ ሴቶች በሴቶች መቆሚያ ይቆማሉ፡፡
ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ሴቶች ቤተ ክርስቲያን ሲገቡ ራሳቸውን መከናነብ አለባቸው፡፡ 1ኛ ቆሮ 11፡5
በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ የሚፈጸሙ ብዙ ሥርዓቶች አሉ
በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ከሚፈጸሙት ሥርዓቶች ጥቂቶቹ እንደሚከተለው ተገልጸዋል፡፡
በቅዳሴ ጊዜ ለቅዳሴ ከተሰየሙት ልዑካን በስተቀር መውጣት፣ መግባት፣ መዘዋወር አይፈቀድም፡፡ የተቻለው ተሰጥዎውን መቀበል ያልተቻለው በጽሙና ሆኖ ጸሎተ ቅዳሴውን መከታተል ያስፈልጋል፡፡ በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ “ስግዱ ለእግዚአብሔር በፍርሃት” (ለእግዚአብሔር በፍርሃት ስገዱ) ይላል ሁላችንም በግምባራችን ተደፍተን እንሰግዳለን ቄሱ ፍትሐት ዘወልድ ይደግማሉ በመቀጠል ዲያቆኑ በእንተ ቅድሳት ይደግማል፡፡ ከዚያም ዲያቆኑ
“ተንሥኡ ለጸሎት” (ለጸሎት ተነሡ) ይላል ሰግደን የነበርነው እንነሳለን ይህ ምሳሌ አለው፡፡ ስገዱ ሲለን መስገዳችን በኃጢአት የመውደቃችን ምሳሌ ነው ተነሡ ሲለን መነሣታችን ደግሞ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስበከት ለአድባራትና ገዳማት የሒሳብ ሠራተኞች ሁለተኛ ዙር የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና መስጠት ጀመረ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሒሳብና በጀት ዋና ክፍል እየተዘጋጀ ሲሰጥ የቆየው የአድባራትና ገዳማት የሒሳብ ሠራተኞች የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና ለሁለተኛ ዙር ተጠናክሮና ተሻሽሎ ለሠልጣኝ ሠራተኞች እየተሰጠ መሆኑ ታወቀ፡፡የሁለተኛው ዙር ሰልጣኝ ሠራተኞች ቁጥራቸው ሰላሳ የሚደርስ ሲሆን ሦስቱ ሠልጣኞች የሀገረ ስበከቱ ሠራተኞች ናቸው፡፡ ሠልጣኝ ሠራተኞች በሥልጠናው የሚቆዩት ለአንድ ወር ብቻ ሲሆን የመጀመሪያው ዙር […]
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት በሥራ እንቅስቃሴያቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አድባራትና ገዳማት የማበረታቻ ሽልማት አበርከተላቸው
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስና የሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት በልማት፣በመልካም አስተዳዳርና በፐርሰንት ክፍያ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ አድባራትና ገዳማት የዋንጫ ሽልማት አበርክቶላቸዋል፡፡ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት በአደስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሥር ካሉት ሰባት ክፍላተ ከተሞች አንዱ ሲሆን በምዕራብ አዲስ አበባ፣ የኦሮምያ ክልል ልዩ ዞን የቡራዮ አስተዳደርና የሰበታ አስተዳደር የሚያዋስነው የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ነው፡፡
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሃያ ሰባት አድባራትና ገዳማት የሚገኙበት ነው፡፡ የክፍለ ከተማ ቤተ ክህነቱ በሰለጠነ የሰው ኃይል የተገነባ መሆኑን በስብሰባው ወቅት ከቀረበው ሪፖርት ለመረዳት ችለናል ÷ በሳምንት አንድ ቀን የሥራና የሠራተኛ ግምገማ እንደሚደረግ ሪፖርቱ አክሎ አብራርቷል ÷ በሪፖርቱ ላይ እንደተዘረዘረው ያለ በቂ ምክንያት ከሥራ የታገዱ ሠራተኞችም ወደሥራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡በዝቅተኛና ያለጨረታ የተከራዩ የአብያተ ክርስቲያናት ቦታዎችም የኪራይ ውላቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡
ሰላምን የሚአደፈርሱና ሁከት የሚፈጥሩ አንድ አንድ ወገኖች ከመጥፎ ድርጊታቸው እንዲታቀቡ የምክር አገልግሎት እየተሰጣቸው ነው፡፡ የምርጫ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ የሰበካ ጉባኤ አባላት በአዲስ ተመራጭ እንዲተኩ ተደርጓል፡፡ የፐርሰንት ክፍያ ከፍ እንዲል ተደርጓል፡፡ ዕውቅና ያልተሰጣቸው ሰባክያን የወንጌል አገልግሎት እንዳይሰጡ የተደረገ ሲሆን ሕጋዊ የሆኑ ሰባክያን ግን የወንጌል ትምህርት እንዲሰጡ ሁኔታዎች ተመቻችተዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያናችን ተተኪ ትውልድ ለማፍራት ወጣቶች 30 ዓመት እስኪሞላቸው ድረስ በሰንበት ት/ቤቱ እየተማሩ እንዲአድጉ በትጋት እየተሠራ ነው፡፡
ከዚህም ጐን የቅርስ ጥበቃ የልዩ ልዩ ልማት እንቅስቃሴ፣እየተከናወነ ነው፡፡ በ2008 ዓ.ም የበጀት ዓመት በሩብ ዓመት ውስጥ ብር4,000,000 አራት ሚሊዮን ብር የፐርሰንት ክፍያ ገቢ ተደርጓል ÷ በክፍለ ከተማው ያገጣሙ ችግሮችን በተመለከተ የኮምፒውተር ጸሐፊ፣ መዝገብ ቤት፣ ተላላኪ አለመመደቡ፣ የትራንስፖርትና የቢሮ ቁሳቁስ አለመሟላት፣ በአንድ አንድ አድባራትና ገዳማት የሚገኙ የሰበካ ጉባኤ ሊቃነ መናብርት በዕንቢተኝነት የደመወዝ ፊርማ አለመፈረም፣ አንድ አንድ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች የቃለ ዓዋዲውን ሕግ ጠብቀው አለመሥራት አንድ አንድ ማህበራት በማይመለከታቸው ጉዳይ ጣልቃ በመግባት የአስተዳደር ሥርዓቱን ለማወክ የሚደረገው ሴራ ዋና ዋና ችግሮች
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘት ጠንክሮ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ
በመ/ር ሣህሉ አድማሱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘትና የተሻለ የሥራ መነቃቃትን ለመፍጠር በማሰብ ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ጀምሮ እስከ አድባራትና ገዳማት የደረሰ የሠራተኛ ዝውውር ተግባር እያከናወነ መሆኑን ተገልጿል፡፡ ሀገረ ስብከቱ ሥራና ሠራተኛን ለማገናኘት ባለው ቁርጥ አቋም መሠረት ከሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ከአንዱ የሥራ ክፍል ወደ ሌላው ሥራ ክፍልና ወደ […]
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባስመዘገበው የዕንግዳ አቀባበል የሥራ ጥራት ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ የማበረታቻ ምስጋና ደብዳቤ ተቀበለ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በ2008 ዓ.ም የተከበረውንና በዩኒስኮ የቅርስ መዝገብ የተመዘገበውን የመስቀል ደመራ በዓል አስመልክቶ የጉብኝት ተግባር ለማከናወን ወደ ሀገራችን በዕንግድነት የመጡት የአሌክሳንደርያ ፖፕና የመንበረ ማርቆስ ፓትርያርክ የሆኑት ብፁዕ ወቅዱስ ታዎድሮስ ሁለተኛ፣ በተጨማሪም ቅዱስነታቸውን አጅበው የመጡት ሊቃነ ኤጲስ ቆጶሳት፣ የልዑካን ቡድን ባደረጉት ሀገር አቀፍ ጉብኝት ላይ ሀገረ ስብከቱ ለጉብኝቱ መሳካት […]
ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በአዲግራት አድባራትና ገዳማት ሲያከናውኑ የቆዩት የአምስት ተከታታይ ቀናት ሐዋርያዊ ጉብኝት ተጠናቀቀ!!
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ከሊቀ ማዕምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ፣ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች፣ ከሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎችና ከአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪች ጋር በመሆን ከጥቅምት 25 ቀን እስከ ጥቅምት 29 […]
ቅዱስ ፓትርያርኩ ተወልደው ያደጉበትን አካባቢ እና የሐውዜን ከተማን ተዛውረው ጎበኙ
ቅዱስነታቸው ክርስትና የተነሱበት ደብር የምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት ጉብኝታቸው ሊጠናቀቀ አምስተኛ ቀኑን ባስቆጠረው የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት ሐዋርያዊ ጉብኝት የተወለዱበትን፣ የተማሩበትን እና በደርግ ዘመነ መንግሥት ከ2,500 በላይ ወገኖችና ከ20,000.00 በላይ እንስሳት በቦንብ ተደብድበው መሥዋዕት የሆኑበትን የሐውዜን ከተማን ተዘዋውረው ተመልክተዋል አባታዊ […]
ቅዱስ ፓትርያርክ የአዲግራት ዩኒቨርስቲን ጎበኙ
የአዲግራት ዩኒቨርስቲ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል ብፁዕ ወቅዱ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነጳጳሳት ዘኢትዩጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የምሥራቅ ትግራይ ሀገረ ስብከት የጉበኝታቸው አንዱ አካል የሆነውን የአዲግራት ዩኒቨርስቲን ጥቅምት 27 ቀን 2008 ዓ.ም ምሽት ላይ ጎበኝተዋል፡፡የዩኒቨርስቲውን አጠቃላይ ይዞታ ፣የማሪዎችን ዶርምተርና የመመገቢያ ቦታዎችን በመኪና በመዘዋወር የተመለከቱት ቅዱስነታቸው ዩኒቨርስቲ የሚጠቀምበትን የዘመናዊ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ማዕከል እና ማዕከሉ የሚጠውን […]
የአዲግራት ደብረ መድኃኔት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ተከበረ
ቅዱስ ፓትርያርኩ በደብሩ ተገኝተው አባታዊ ምክር ሲሰጡ በአዲግራት ከተማ በምሥራቃዊ ዞን ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የአዲግራት ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ቅዳሴ ቤት በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ ተባርኮ የተመረቀ ሲሆን ቅዱስ ፓትርያርኩ ይህ ሕንፃ ከተራ ቤትነት ወደ ተቀደሰ ቤተ ክርስቲያንነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሃይማኖታዊ ቀኖና መሠረት ተለውጧል፡፡ስለሆነም የአከባቢው ህዝበ ክርስቲያን በገንዘቡ […]
ከካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጋር ያለን የሃይማኖት ልዩነት እንደተጠበቀ ሆኖ ለሀገር ልማት በጋራ መሥራት እንደሚገባ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ አሳሰቡ
ብፁዕ አቡነ ተሥፋ ሥላሴ የወርቅ ፅዋ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ሲያበረክቱ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቀ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የምሥራቅ ትግራይ ዞን ሐዋሪያዊ ጉዞን በማስመልከት የትግራይ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ተስፋ ሥላሴ፤ካህናት፣ ምዕመናንና በካቶሊክ ቤተክርስቲያን የሚማሩ ተማሪዎች ከአዲግራት ከተማ 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ አቀባበል አድረገውላቸዋል፡፡የአዲግራት ከተማ ሕዝበ […]