• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

0027

ተቀፀል ፅጌ አጼጌ

በየዓመቱ መስከረም 10 ቀን ሲከበር የቆየው የተቀ    ፀል ፅጌ በዓል በዘንድሮውም ዓመት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎች፣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአድባራትና ገደማት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮአል፡፡በበዓሉ ላይ ጥንግ ድርብ የለበሱ ካህናት፣ዩኒፎርም […]

054953

በቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ቅዱስ ገብርኤል ቤተክረስቲያን ይልማት እንቅስቃሴ እየተድረገ መሆኑ ተገለፀ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በአዲሱ ስም ትጠሪያለሽ ት/ኢሳ  62፣2 ነበየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳያስ ስለ ፅዮን ወይም ስለ እየሩሳሌም መታደስ ስለሚመጣው ብርሃኗና የህይዎቷ ፋናዋ አስቀድሞ በትንቢት ሲናገር‹‹ ስለ ፅዮን ዝም አልልም ስለ  እየሩሳሌ ምን ፀጥ አልልም  ጽድቋ እንደጸዳል መዳኗም እንደሚበራ  ፋና እስኪ ወጣ ድረስ ለህዝቡ ጽድቅሽን ነገስታትም ሁሉ ክብርንሽን ያያሉ……በአዲሱ ስም ትጠሪያለሽ በማለት በተነበየው […]

0023

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን አዲሱን ዓመት አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

ከሁሉ በፊት ባንድነትና በስምምነት ጠብቆ ከዘመነ ማርቆስ ወደ ዘመነ ሉቃስ (2007 ዓ.ም) ያሸጋገረን አምላክ የተመሰገነ ይሁን፡፡   በመቀጠልም ሕዝበ ክርስቲያኑን እንኳን ለ2007 ዓ.ም አዲሱ ዓመት አደረሳችሁ እላለሁ፡፡ አዲሱ ዘመን የሰላም፣የአንድነት፣የፍቅርና የብልጽግና ዘመን እንዲአደርግልን እየተመኘሁ በ2006 ዓ.ም የተሠሩ ሥራዎችን በመገምገም ማለትም በቢሮም ሆነ በተናጠል ምን ሠራሁ? ምን አቅጄ ነበር? ምንስ አሣካሁ? ያላሳካሁትስ ምንድነው? የገጠመኝ ፈተናስ ምንድነው? የገጠመኝ […]

0908

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2007 ዓ.ም የዘመን መለወጫ መልእክት አስተላለፉ

መልእክት ዘእምኅበ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በእንተ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዓቢይ ዘዕሥራ ምእት ወሰብዓቱ ዓመተ ምሕረት፤በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን•    በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤•    ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትኖሩ፤•    የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤•    በሕመም […]

0056

ብፁዕ ወቅዲስ ፓትርያርኩ የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ለሚያስገነባቸው ሁሉገብ ሕንጻዎች የመሠረት ደንጊያ አስቀመጡ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎችና የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ሰኞ ነሐሴ 19 ቀን 2006 ዓ.ም ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው ዘውዲቱ ሕንጻና መንበረ መንግሥት ሕንጻ ጎን የድርጅቱ ይዞታ በሆነው ክፍት ቦታ ላይ ተጨማሪ ሕንጻዎችን ለመገንባት  […]

0131

የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የዘመኑን ፐርሰንት ክፍያ ላጠናቀቁ አድባራትና ገዳማት ሽልማት ሰጠ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የ2006 ዓ.ም የበጀት ዓመት የፐርሰንት ክፍያ እስከ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ሙሉ በሙሉ በመክፈል መንፈሳዊ ኃላፊነታቸውን በተገቢው መንገድ የተወጡ አድባራትና ገዳማት ከክፍለ ከተማው ቤተ ክህነት የተዘጋጀ ሽልማት የሀገረ ስብከቱ ዋና ስራ አስከያጅ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን ፣የሀገረ ስብከቱ ምክትል ስራ አስከያጅ መምህር ኃይለማርያም አብርሃ […]

0908

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የ2006 ዓ.ም. ጾመ ፍልሰታን አስመልክተው መልእክት አስተላለፉ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜንየተወደዳችሁ በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትኖሩ ሕዝበ ክርስቲያን በአጠቃላይ እግዚአብሔር አምላክ እንኳን ለ2006 ዓ.ም ጾመ ማርያም በሰላም አደረሳችሁ፡፡‹‹ወዘሰ እንተ አንቀጽ ይበውእ ኖላዌ ዓባግዕ ውእቱ፤ በበሩ የሚገባ የበጎች እረኛ ነው›› (የሐ 10 ÷ 2)በብሉይ ኪዳን የበጎች እውነተኛ እረኛ እንደሆነ በብዙ ስፍራ የተነገረለት መሢሕ አንድ ቀን በዓለም እንደሚገለጽና በጎቹን በትክክል […]

d0012

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ም/ሥራ አስኪያጅ ተመደበ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከጥቅምት ወር 2005 ዓ.ም በፊት በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ፤ በዋና ሥራ አስኪያጅና በም/ሥራ አስኪያጅ ይመራ ነበር ሆኖም ግን በጥቅምት ወር 2005 ዓ.ም ሀገረ ስብከቱ የተሻለ የሥራ አመራር ሂደትን ሊያመጣ ይችላል በማለት በ4 አህጉረ ስብከት ተከፍሎ እስከ ግንቦት 2005 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  የዘለቀ ሲሆን ሀገረ ስብከቱ እንደገና ወደ […]

d0988

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ፣ ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት በሰርተፍኬት፣ በዲፕሎማ፣ በድግሪ እና በማስተርስ አስመረቀ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ቅዳሜ ሰኔ 28 ቀን 2006 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ጥሪ የተደረገላቸው ዕንግዶች እና የተመራቂ ደቀመዛሙርት ቤተሰቦች በተገኙበት ተመራቂ ደቀመዛሙርትን በሰርተፍኬት፣ በዲፕሎማ፣ በድግሪና በማስተርስ ያስመረቀ ሲሆን  በርቀት መርሐ ግብር በሰርተፍኬት 83፣ […]

0153

የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት በዲፕሎማ አስመረቀ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰዋስወ በርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ በማታውና በቀን መርሐ ግብር ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት ቅዳሜ ሰኔ 21 ቀን 2006 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን