• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

2326

የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ጥያቄና የሀገረ ስብከቱ ዋናሥራ አስኪያጁ በሳል አመራር!!

 ማክሰኞ ሰኔ 2 ቀን 2007 ዓ.ም ከጧቱ አራት ሰዓት ጀምሮ አራት ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ከአጥሩ ግቢና ከአጥሩ ውጭ ባለው ከሜዳ ላይ ዩኒፎርም የለበሱና በመቶወች የሚቆሩ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች በሜዳው ላይ በመትመም ጭብጨባና ከበሮ የተለየው ዝማሬ ያሰማሉ፡፡ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በር ላይ እንዲህ አይነቱ የወጣቶች ዝማሬ አልፎ አልፎ […]

2284

የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃነጳጳሳትና የምእመናን ልኡካን ቡድን በሊቢያ አሸባሪ ቡድን የተሰውትን ሰማዕታት ቤተሰቦች አፅናኑአቸው!!

ብፁዕ አቡነ የሱፍ በሰሜን አሜሪካ የግብፅ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ቢመን በግብፅ የናካዳ እና ቆስ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ካራስ በግብፅ የማሓላዘኮብራ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እና ቁጥራቸው ከሃያ ያላነሱ ግብፃውያን ምዕመናን እሁድ ግንቦት 23 ቀን 2007 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ በመገኘት በሊቢያ በአሸባሪ ቡድን የተሰውትን ሰማዕታት ቤተሰቦች በወንጌል ትምህርት አፅናንተዋቸዋል፡፡ […]

1936

የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤተክርስቲያን አንደኛ ደረጃ፣ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ት/ቤት ለሦስት ዓመታት ባስመዘገበው ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ከአስር ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ መሆኑ ተገለፀ

በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ቤተክርስቲያን አንደኛ ደረጃ፣ሁለተኛ ደረጃና መሰናዶ ትምህርት ቤት ላለፉት ሶስት ዓመታት ባስመዘገበው ከፍተኛ የሥራ አፈጻጸም ከግል ት/ቤቶች ከአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ 1ኛ፣ከአዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ደረጃ ከተመረጡ አስር ትምህርት ቤቶች መካከል አንዱ በመሆን የዋንጫ ተሸላሚ በመሆኑ ሐሙስ ግንቦት 13 ቀን 2007 ዓ/ም በደብሩ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ውስጥ የአዲስ አበባ […]

2022

የቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሁለገብ ሕንጻ ግመንባታ በመጠናቀቁ በይፋ ተመረቀ!!

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሁለገብ ሕንጻ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ብፁዕ አቡነ ማትያስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ክቡር ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ ሊቀማዕምራን […]

0048

በአዲስ አበባ ከተማ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ቁጥራቸው ከስድስት መቶ ካላነሱ የሃይማኖት ተወካዮች ጋር የአንድ ቀን የጋራ ውይይት አካሄዱ

በአዲስ አበባ ከተማ የሃይማኖቶች ተቋማት ጉባኤ ወጣቶች ለሰላም ያላቸውን ሚና እና የሽብር ቡድኖችን እኩይ ተግባር አስመልክቶ ቁጥራቸው ስድስት መቶ ለሚደርስ ከሃይማኖቶች ተወካዮች ጋር ማክሰኞ ግንቦት 4 ቀን 2007 ዓ.ም ሜክሲኮ በሚገኘው የተግባረ ዕድ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ለአንድ ቀን የቆየ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት ተካሄዷል፡፡ ጉባኤው የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ በሆኑት በሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ የተመራ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማትን […]

640

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የመልካም አስተዳደር አተገባበር

በአንድ መሥሪያ ቤት /ድርጅት/ ውስጥ ከሚያስፈልጉ ቁልፍ ጉዳዮቸ መካከል ቀዳሚ ሊባል የሚችለው መልካም አስተዳደር እንደሆነ የማህበረሰብ ምሁራን ይናገራሉ፡፡ በእንዚህ መሁራን ምልከታ መሠረት በአገልጋይና ተገልጋይ መካከል  በመተማመን ላይ የተመሠረተ ግንኙነት ሊፈጠር የሚችለው መሥስሪያ ቤቱ /ድርጅቱ/ አስተማማኝ የመልካም አስተዳደር ሁኔታን መገንባት ሲችል ብቻ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በተለይም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ያለው የሰው ኃይል […]

2021

የ2007 ዓ.ም.የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠናቀቀ

ሚያዝያ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በጸሎት የተጀመረው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲካሔድ ቆይቶ ዛሬ ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ረፋድ ላይ ተጠናቅቆ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቷል፡፡በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜንከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫበፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 ላይ በተደነገገው ቀኖና ቤተ ክርስቲያን […]

346

የ2007 ዓ.ም.የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጀመረ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱ-ስ አሐዱ አምላክ አሜን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትምሕረትና ይቅርታ፣ ትዕግሥትና ቸርነት የባህርዩ የሆነ እግዚአብሔር አምላክ፣ ሰፊውን የወርኃ ጾም አገልግሎት በሰላም አስፈጽሞ ብርሃነ ትንሣኤውን በሰላም ስለአሳየን፣ እንደዚሁም ሃይማኖታዊ፣ ቀኖናዊና ዓመታዊ ከሆነ ከዚህ የረክበ ካህናት ጉባኤ በሰላም ስላደረሰን ክብርና ምስጋና ለእርሱ እናቀርባለን፡፡ ‹‹ኀበ ሀለዉ ክልኤቱ ወሠለስቱ ጉቡአን በስምየ አነ እሄሉ ማእከሌሆሙ […]

00011

በሊቢያ ለተሰዉት ሰማዕታት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ፍትሐት ተካሔደ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፤ የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የግብጽ አምባሰደር፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ የሰማዕታቱ ቤተሰቦችና ምእመናን በተገኙበት ጸሎተ ፍትሐቱ ተከናውኗል፡፡ቅዱስ ፓትርያርኩ ያስተላለፉትን መልእክት ቀጥሎ እናቀርባለን፡፡በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ አሜን!ዘሰ አምነኒ በቅድመ ሰብእ አነኒ አአምኖ በቅድመ አቡነ ዘበሰማያትበሰው […]

346

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2007 ዓ.ም. የትንሣኤ በዓልን አስመልክተው መልእክት አስተላለፉ

346

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በእንተ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት፡፡
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ፡፡
– በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣
– ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤
– የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤
– በሕመም ምክንያት በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
– እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት፤
በሞትና በመቃብር ላይ ሥልጣን ያለው ኃያሉና አሸናፊው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ ፡፡
‹‹ወበከመ በእንተ አዳም ኵልነ ንመውት ከማሁ በክርስቶስ ኵልነ ነሐዩ፤ ሁላችን በአዳም እንደምንሞት እንደዚሁም ሁላችን በክርስቶስ ሕያዋን እንሆናለን›› (1ቆሮ. 15÷22)፡፡
እዚህ ላይ በተገለፀው ቃለ እግዚአብሔር መሠረት የሰዎች መጻኢና የመጨረሻ ዕድል ከሁለት አዳማዊ ውርስ ጋር የተያያዘ ሆኖ ይገኛል ፡፡
በቅዱስ መጽሐፍ በግልጽ እንደተጻፈው ሰው ሁሉ ከቀዳማዊ አዳም በሥጋ ተወልዶአል፤ የእርሱ የሆነውንም ሁሉ ወርሶአል፤ይህም ማለት በሥጋው በኩል የግብረ ኃጢአት ዝንባሌን፣ ሞተ ሥጋን፣ ወሪደ መቃብርን፣ በመቃብር ውስጥ መበስበስንና መፍረስን ሲወርስ በነፍሱ በኩል ደግሞ ከእግዚአብሔር መለየትን፣ በኃጢአት ተሸንፎ የዲያብሎስ ሎሌ መሆንን፣ በኃጢአቱ ምክንያት ለኵነኔ ሲኦል ተጋላጭ መሆንን እና የመሳሰሉትን ሁሉ ወርሶአል ማለት ነው፡፡
ጠቅለል አድርገን ስናየው ቀዳማዊ አዳም በሥጋና በነፍስ ከባድ ውድቀትን ለልጆቹ አውርሶአል ማለት ነው ፡፡
ከቀዳማዊ አዳም የውድቀት ዘመን ጀምሮ

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን