• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ርዕሰ ዓውደ ዓመት የአዲስ ዘመን መጀመሪያ

በኢትዮጵያ ያለፈው ዓመት አልቆ የሚተካው የሚጀመርበት መስከረም አንድ ቀን እንደ ቤተክርስቲያናችን ትውፊት ርዕሰ ዓውደ ዓመት የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ዘመን ሲያልፍ ዘመን ይተካል፡፡ ትውልድም ሲያልፍ ትውልድ ይተካል፡፡ ለኅልፈትና ለውላጤ የተፈጠረ ፍጡር ሁሉ ወቅትና ጊዜ አለው፡፡ በዚያው በተሰጠው ዘመን ሁሉም ሥራውን ያከናውናል፡፡ አከናውኖም ያልፋል ያለሥራ የተፈጠረ ፍጡር የለምና፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረታትን ፈጥሮ ሲፈጽም ‹‹ወርእየ እግዚአብሔር ኵሎ ዘገብረ […]

0265

የመንበረ ጸባዖት ቅዱስ በዓለ ወልድ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን እድሳት ተጠናቆ ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ በአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ሥር የሚገኘው የመንበረ ጸባዖት ቅዱስ በዓለ ወልድ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ከዕድሜ ብዛት የተነሣ የሕንጻው መዋቅሮች በመናጋት ደረጃ ላይ የደረሱ በመሆናቸው የካቴድራሉ የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት ባደረገው ያላሰለሰ ክትትል በአሥራ አንድ ወራት ውስጥ በተደረገ የጥገና እና የዕድሳት ሥራ 2,990,460.32 ብር  ወጪ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ […]

0669

ቁጥራቸው ከ3,000 በላይ የሚገመት በደቡብ ኦሞ የዳንሰነች ማኅበረሰብ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነትን በመቀበላቸው ጥምቀተ ክርስትና ተፈጸመላቸው

መሠረቷ ብሉይ ኪዳን፣ ጉልላቷ ሐዲስ ኪዳን የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕገ ኦሪትን በዘጠኝ መቶ ዓመተ ዓለም በቀዳማዊ ምኒሊክ አማካኝነት ተቀብላ አምልኮተ እግዚአብሔርን ስታስፋፋ ከቆየች በኋላ አዲስ ኪዳንን ደግሞ በ34 ዓመተ ምሕረት በጃንደረባው /ባኮስ/ አማካኝነት የተቀበለች ሲሆን ሥርዓተ ክህነትን በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን በአባ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን /ፍሬምናጦስ/ በኩል ተቀብላ ክርስትናን ስታስፋፋ ቆይታለች፡፡ ጌታችንና […]

pp009

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የ2009 ዓ.ም ጾመ ፍልሰታን አስመልክተው መልእክት አስተላለፉ

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በእንተ ጾመ ፍልሰታ ለማርያም ዘዕሥራ ምዕት ወተስዐቱ ዓመተ ምሕረት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን + በሀገር ውስጥና በተለያዩ ክፍለ ዓለማት የምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ!! + እኛን ለክብርና ለምስጋና የፈጠረ […]

a0017

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የ2009 ዓ.ም በሰባቱ ክፍላተ ከተማ ዓመታዊ የሥራ ግምገማ አካሄደ

ሀገረ ስብከቱ ከሰባቱ ክፍላተ  ከተማ ቤተ  ክህነት የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር  በ2009 ዓ.ም የበጀት ዓመት የተከናወኑትን የልማትና የፐርሰንት ገቢ አስመልክቶ ሐምሌ 28 ቀን 2009 ዓ.ም ባደረገው አጠቃላይ ዓመታዊ ሪፖርት ላይ የተመሠረተ የምክክርና የመገማገም ሥራ  አከናውኗል፡፡ ሀገረ  ስብከቱ  በዚሁ ወር መግቢያ  በፐርሰንት  አሰባሰብ ዙሪያ  ሰፋ  ያለ  ውይይት  እና  ግምገማ ያካሄደ መሆኑ  ይታወቃል፡፡ በሰባቱም  ክፍላተ ከተማ  በየተራ  […]

መልካም ባልንጀራ

ምስጢር የሚወያዩትን አብሮ የሚሠሩትንና ጧት ማታ የሚገናኙትን እንዲሁም አብሮ አደግ የሆነውን ሰው ባልንጀራዬ ነው ብሎ መናገር የተለመደ ነው፡፡ ዛሬ ለኔ ነገ ላንተ እየተባባሉ አብረው ከሚውሉት፣ ከሚያመሹት ጓደኞቻቸው ሌላ ባልንጀራ ያለ የማይመስላቸውም ብዙዎች ናቸው፡፡ በመሠረቱ አብሮ መብላትና መጠጣት ወይም በአንድ ላይ ተምሮ ማደግና አብሮ መኖር ይልቁንም ትንሽ ትልቁን ክፉና ደጉን ምስጢር መካፈል ባልንጀራ ሊያሰኝ ቢችልም ይህ […]

pp002

የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በቅጥረ ግቢው መካነ መቃብር ዙሪያ በሶሻል ሚዲያ ላይ ለተሰራጨው መሠረተ ቢስ ዘገባ ማብራሪያ ሰጠ

በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እና በበዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን መካነ መቃብራት የሚገኙ ዐፅሞች እንዲፈልሱ የተወሰነው፣ በቦታው ሕንፃ ለመሥራት ተፈልጎ ሳይሆን፤ የመቃብር ቦታው በመሙላቱና በመጨናነቁ እንደሆነ የካቴድራሉ አስተዳደር አስታወቀ፡፡ ሊቀ ሥልጣናት አባ ገብረ ሥላሴ በላይ፣ የቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እና የበዓለ ወልድ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ፣ ስለ ጉዳዩ ከሰንደቅ ጋዜጣ ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ፥ መካነ መቃብራቱን ከማልማት፣ ከማስዋብና […]

1018

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የነበረው ሥልጠና ባለ 14 ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ

ሙሉ ዝርዝሩን ከዚህ ቀጥሎ እንደሚከተለው ይቀርባል በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ዋና አዘጋጅነት እና በኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማህበር ትብብር በሥሩ ለሚገኙ የሀገረ ስብከቱ የመምሪያ ኃላፊዎች የሁሉም ክፍለ ከተማ የክፍል ኃላፊዎች የአብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎችና ዋና ፀሐፊዎ የሙያ ማጠናከሪያ ሥልጠና ቃለ ጉባኤና የአቋም መግለጫ የስልጠናው መሪ ክቡር መምህር ጎይቶም ያይኑ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ […]

09240

የአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች የሙያ ማሻሻያ ሥልጠና መስጠት ጀመረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ከሰኔ 19-23 ቀን 2009 ዓ.ም ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የሥራ ፈጠራ፣ የሊደርፕ ማኔጅመት፣ ሕግ፣የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት እና ስርጭት ሥልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡ ከኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኀበር ተወክለው ሥልጠናውን የሚከታተሉት  መ/ር አቢይ ሀረጉ በማኅበሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዴስክ ኃላፊ በስተላለፉት መልእክት […]

0808

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በተለምዶ 22 እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በመገንባት ላይ ያለውን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሁለገብ ሕንጻ ጎበኙ!!

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተለምዶ 22 ሁለት እየተባለ በሚጠራው አካባቢና ጎላጎል ሕንጻ ጎን እየተገነባ የሚገኘውን የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሁለገብ የልማት ሕንጻ አርብ ሰኔ 2 ቀን 2009 ዓ.ም ከቦታው ድረስ ተገኝተው ጎብኝተዋል፡፡ የጉብኝቱ መርሐ ግብር በተካሄደበት በዚሁ ዕለት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የአዲስ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት