• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

640

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልዕኮ ዋና ክፍል የወጣ ክፍት የሥራ ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሲሠራበት የነበረውን ለማዳዊ አሠራር ወደ ዘመናዊ የአስተዳደር ሲስተም መቀየሩን ተከታትሎ አመርቂ ውጤት ከተገኘባቸው የሥራ አይነቶች መካከል የሠራተኛ ቅጥርና ዝውውር እንዲሁም የዕድገት አሰጣጥ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው፡፡ ሀገረ ስብከቱ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን በወሰዳቸው እርምጃዎች ካለፈው መጋቢት ወር ጀምሮ መምህራንን፣ ካህናትንና ዲያቆናትን አወዳድሮ መቅጠር በመጀመሩ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብሎም ምእመናን […]

000340

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ክርስትና ካልተስፋፋባቸው ብሔር ብሔረሰቦች ካህናትን ለማፍራት እየሠራ ነው

ፎቶ ፋል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ክርስትና ያልተስፋፋባቸው የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ወንጌለ መንግሥተ ሰማያትን ለማስፋፋት ከየብሔረሰቡ ካህናትን ለማፍራት ተግቶ እየሠራ መሆኑ ተገለፀ፡፡የሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ እንደገለፁት ከጋምቤላ ክልል 18 ከደቡብ ሱዳን 3 ደቀመዛሙርትን መልምሎ ከትውልድ አካባቢያቸው ድረስ ሄዶ በማምጣት በአዲስ አበባ ከተማ በሰዓሊተ ምሕረት ቅድስተ ማርያም የአብነት ት/ቤት በአደራነት አስገብቶ […]

00230

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ለአህጉረ-ስብከትና ለቤተ ክርስቲያናችን ተቋማት እገዛ እያደረገ ነው

የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ህንፃ በከፊል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ራሱ ካለበት ዘርፈ ብዙ ሥራዎች በተጨማሪ የቤተ ክርስቲያንን ሁለንተናዊ ዕድገት ለሚያፋጥኑ እንዲሁም ወቅታዊ ችግር ላለባቸው አህጉረ ስብከትና የልማት ተቋማት ድጋፍ እያደረገ መሆኑ ተገለፀ፡፡ የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ባለፉት 6 ወራት ብር 8,000,000.00 (ስምንት ሚሊየን ብር) የሚጠጋ ድጋፍ ማድረጉ ታውቋል፡፡ ድጋፍ ከተደረገላቸው ውስጥ በብፁዕ አቡነ ሉቃስ ለሚመራው […]

c001

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በግማሽ ዓመት 74 ሚሊየን ብር ከፐርሰንት ገቢ ሰበሰበ

ፎቶ ፋል የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከአጥቢያ አቢያተ ክርስቲያን ባለፈው ግማሽ ዓመት ብር 74,000,000.00 (ሰባ አራት ሚሊየን ብር) ሰበሰበ፡፡ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ሀገረ ስብከት የሆነው፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ጽ/ቤት በመላው ኢትዮጵያና በውጪ ሀገራት ለሚያደርገው ሐዋርያዊ ተግባር አስፈላጊ የሆነውን ከፍተኛ ገንዘብ የሚያቀርብ ሀገረ ስብከት ሲሆን የዘንድሮ የፐርሰንት አሰባሰቡ በ2007 ዓ.ም ተመሣሣይ ወቅት […]

640

ፈቃድ ሳይሰጣቸው በየገዳማቱና አድባራቱ እየተዘዋወሩ የሚሰብኩ ሰባክያን ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግባቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለገዳማትና አድባራት ጠንከር ያለ የጹሑፉ መመሪያ አስተላለፈ

640

ጥንታዊትና ሐዋርያዊት የሆነችዋ የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሀገራችን ኢትዮጵያን በመንፈሳዊና በማኀበራዊ መስክ ስታገለግል የኖረችና እያገለገለች ያለች መሆንዋን የገለጸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በአገልግሎቱ ከሚሳተፉ አካላት ብዛትና ከቁጥጥር ማነስ የተነሳ አንድ አንድ ችግሮች እየተፈጠሩ ስለሆነ እነዚህን ችግሮች ለመቅረፍና ስብከተ ወንጌል በተሻለ ስፋትና ጥራት ባለው ፣ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን በጠበቀ መልኩ ማስፋፋት ይቻል ዘንድ በቁጥር 1177/482/07 27/03/08 በተጻፈ ደብዳቤ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ ገዳማትና አድባራት መመሪያ አስተላልፎል፡፡
በመሆኑም በርካታ ገዳማትና አድባራት በተላለፈው መመሪያ የስብከተ ወንጌሉን መዋቅር እየጠበቁና እያስጠበቁ የሚገኙ ሲሆን አንድ አንድ ኃላፊነታቸውን የዘነጉ የገዳማትና አድባራት የሥራ አመራሮች መመሪያውን ወደ ጐን በመተው ሕጋዊ ያልሆነ ተግባር ሲፈጽሙ የታዩ ሲሆን ሀገረ ስብከቱ በእነዚህ ኃላፊነታቸውን በዘነጉ የገዳማትና አድባራት የሥራ አመራር ላይ አስፈላጊውን ሕጋዊ ርምጃ እየወሰደ መሆኑን የሀገረ ስብከቱ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ሰላም ዳዊት ያሬድ ገልጸዋል፡፡
ጥር 17 ቀን 2008 ዓ.ም የነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት በልማትና በፐርሰንት ክፍያ ላቅ ያለ ውጤት ላስመዘገቡ አብያተ ክርስቲያናት በያዘው የመሰጋገኛና የማበረታቻ ሽልማት መርሐ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ የሌላቸውና ኢሕጋውያን የሆኑ ሰባክያንን አስመልክቶ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ባቀረቡት ገለፃ ያልተፈቀደላቸው ኢህጋውያን ሰባኪን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በቁጥር 3075/90/04 በቀን 18/08/04 ዓ.ም ተደጋጋሚ ውሣኔዎችን ያሰተላለፈ መሆኑን በመጥቀስ በስብከተ ወንጌል ስም እየተቧደኑ የቤተ ክርስቲያንን ሰላም ለማናጋት በየጊዜው የሚወጡ፣ የሚወርዱ ፣የሚጥሩ ግለሰቦች አፍራሽ ተልእኮ እየፈጸሙ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ብፁዕ ወቅዱስ ፖትርያርኩም ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት እነዚህ ኢሕጋውያን ሰባክያን፣ከአንዱ ወደ ሌላው እየዘለሉና እየተፈናጠሩ ለሕዝብ ጥቅም ሳይሆን ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ በቤተክርስቲያናችን ሰላምና አንድነት ላይ ችግር ለማድረስ እየጣሩ ስለሆነ የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ልጆቻችን ቤተክርስቲያናቸውን ነቅተው ሊጠብቁ ይገባቸዋል፡፡ አንዳንዶቹ ከሀገር ውጭና ከሀገር ውስጥ በመዘዋወር የሃሳብ አቅጣጫቸውን እየቀያየሩ የሚሠሩ ሰዎች ናቸው፡፡ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ቃሉ “ ወእምፍሬሆሙ ተአምርዎሙ” ከፍሬአቸው ታውቋቸዋላችሁ ብሎ እንደአስተማረን ከድርጊታቸው ግንዛቤ በመውሰድ ቅድስት ቤተክርስቲያንን ነቅተንና ተግተን ልንጠብቅ ይገባናል ብለዋል፡፡
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለገዳማትና አድባራት ያስተላለፈውን ጥብቅ መመሪያ ሙሉ ሐሳቡን እንደሚከተለው

0544

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ለሁለተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን የገዳማትና አድባራት የሒሳብ ሠራተኞች በሠርተፍኬት አስመረቀ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከገዳማቱና አድባራቱ ለተውጣጡ ቁጥራቸው 30 ለሆነ የሒሳብ ሠራተኞች ዘመናዊ የሒሳብ አሠራር፤ የቋሚና የአላቂ ንብረት አያያዝና አወጋገድን አስመልክቶ ለ3 ወራት ያህል የሰለጠኑ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በተገኙበት ሰኞ ጥር 16 ቀን 2008 ዓ.ም በሰርተፍኬት አስመርቋል፡፡ሰልጣኞቹ በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ ባደረጉት ንቁ ተሳትፎ በሀገረ ስብከቱ በኩል ተሻላሚ ሲሆኑ የሰልጣኞችን […]

9090

የ2008 ዓ.ም የጥምቀት በዓል በድምቀት ተከበረ !!!

የጌታችን የመድኃኒታቺን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ በመላ ሀገሪቱ ተከብሮ ውሏል።በዓሉ ኢየሱስ ክርስቶስ  በዮሃንስ እጅ ለመጠመቅ ወደ ባህረ ዮርዳኖስ የወረደበትን ዕለት ለማሰብ  የሚከበር ነው፡፡በተለይም በዓሉ በአዲስ አበባ ጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት በድምቀት በተከበረበት ወቅት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን  ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም […]

የአቃቂ ቃሊቲ የጥምቀት ባህር ቦታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይዞታ ሆኖ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ፈቃድ ሰጠ

የአቃቂ ቃሊቲ የጥምቀተ ባህር ቦታ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፖትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖትና በክቡር አቶ ደሪባ ኩማ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ከንቲባ የጋራ ምክክርና ውይይት በኋላ 25ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ያለው የጥምቀተ ባህር ቦታ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይዞታ ሆኖ እንዲቀጥል […]

0018

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስከያጅ ሊቀ ማእምራን የማነ ዘመንፈስ ቅዱስ የ2008 ዓ.ም በዓለ ጥምቀትን አስመልክተው መልእክት አስተላለፉ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!ከሁሉ በማስቀደም የሁላችንም አስገኚና የሕይወት ምንጭ እግዚአብሔር አምላካችን በሕይወትና በጤና ጠብቆ ለብዓለ ልደቱና ጥምቀቱ ስላደረሰን ምስጋና ይግባው፡፡ አምካችን እግዚአብሔር ከዘመን መለወጫ የቅዱስ ዮሐንስ በዓል እስከ ልደቱና ጥምቀቱ ድረስ በሰጠን ጊዜ በርካታ ነገሮችን አከናውኖልናል፡፡ የጀመርነውን የሒሳብ አሠራር ለውጥ ለማስፋት ሁለተኛ ዙር የሒሣብ ሠራተኞች ሥልጠና በተሳካ ሁኔታ ያጠናቀቅነው ባለፈው አጭር […]

በዓለ ቅድስት ሥላሴ

ሥላሴ የሚለው ቃል ‹‹ሠለሰ›› ሦስት አደረገ ከሚለው የግዕዝ ሥርወ ቃል የተገኝ ሲሆን ይህም ሦስትነት ማለት ነው፡፡ ምሥጢረ ሥላሴ ብለን ስለነገረ ሃይማኖት ስንናነገር ግን አንድም ሦስትም ተብሎ ይተረጎማል፡፡ በዚህም መሠረት እግዚአብሔርን አንድም ሦስትም ብለን ማመናችንን የምንገልፅበት የሃይማኖት ዶግማ ነው፡፡እንደሚታወቀው የሥላሴ አንድነት ስንል በባህርይ በህልውና በፈቃድ…. አንድ አምላክ ማለታችን ሲሆን  ሦስትነት ስንል ደግሞ በስም’ በአካል’ በግብር ነው፡፡የሥላሴ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን