• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

“በዓለ ጥምቀት በኢትዮጵያ”

ከሊቀ ብርሃናት ኢሳይያስ ወንድምአገኘሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኝ ዓበይት በዓላት ውስጥ በየዓmቱ ጥር 11 ቀን በመላዋ ኢትዮጵያ በሚገኙት አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ በገጠርም በከተማም በታላቅ ድምቀት የሚከበረው በዓለ ጥምቀት አንዱ ነው፡፡ ይህም በዓል ከበዓላቱ ሁሉ በላይ በድምቀት የሚከበር ታላቅ በዓል ነው፡፡ የጥምቀትን በዓል አከባበር ከሁሉም በዓላት ለየት ከሚያደርጉትም ምክንያቶችና ሁኔታዎች ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡ […]

pp009

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የ2010 ዓ.ም የልደት በዓልን አስመልክተው መልእክት አስተላለፉ

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በእንተ በዓለ ልደቱ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ ሎቱ ስብሐት!! በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!! -በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ -ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤ -የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤ -በሕመም […]

4521

“ኖላዊሆሙ ለእስራኤል አጽምእ”(የእስራኤል ጠባቂ ሆይ አድምጥ)

  በመ/ር ሣህሉ አድማሱ በቤተክርስቲያናችን የቃለ እግዚአብሔር አሰጣጥ መሠረት ከብርሃን ቀጥሎ ያለው ሳምንት ኖላዊ ተብሎ ተሰይሟል፡፡ ኖላዊ ተብሎ  በሚጠራው ሰንበት “ኖላዊ  ዘመጽአ…” የሚለው የቅዱስ ያሬድ የዜማ ድርሰት በሌሊት  የአገልግሎት ክፍለ ሰዓት በሊቃውንቱ ሲዘመር ያድራል፡፡ በጧቱ በሥርዓተ  ቅዳሴ ወቅት (ዕብ.13÷16)፣ (1ጴ 2÷21)፣ (የሐ.10÷36-43 በዲያቆናትና  በካህኑ  በንባብ ይቀርባል፡፡ የእስራኤል ጠባቂ ሆይ አድምጥ፣ዮሴፍን እንደመንጋ  የምትመራ፣ በኪሩቤል  ላይ የምትቀመጥ ተገለጥ […]

“እውነተኛው የዓለም ብርሃን”

በመምህር ኪዱ ዜናዊ ብርሃን÷ ብርሃን የጨለማ ተቃራኒ ነው፤ ለዚያም ነው ብርሃን የሌለበት ጨለማ ተብሎ የሚጠራው። ጨለማ መኖሩ የሚታወቀው ብርሃን ሳይኖር ሲቀር ነው። ብርሃን በሁለት መልኩ ልንገልጸው እንችላለን÷ ውጫዊ(ዓለማዊ) እና መንፈሳዊ(ውስጣዊ)፤ የመጀመርያው ከተፈጥሮአዊው(ፀሐይ) ወይም ከሰው ሰራሽ የሚገኝ ሲሆን ያንን ብርሃን ወደ ዓይናችን ሲያንጸባርቅ ነገሮችን ማየት እንችላለን፤ ዓይናችን ያ ብርሃን ካላገኘ ግን ጨለማ ነው ምንም ማየት አይችልም። […]

6139

በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የዘመናችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተግዳሮቶችና የመፍትሔ ሃሳቦች በሚል ርእስ ጥናታዊ ጽሁፍ ቀረበ

በአዲስ አበባ ሀ/ስብከትና በሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ መምሪያ በተደረገ የጋራ ዝግጅት የዘመናችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ተግዳሮቶችና  የመፍትሔ ሃሳቦች በሚል ርእስ የተጠና ጥናታዊ ጽሑፍ የሃገረ ስብከቱ ሥራ አስክያጅ መ/ር ጎይትኦም ያይኑ፤የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣የየአድባራቱ ሰባክያነ ወንጌል ሐላፊዎች፣ ሊቃነ መናብርትና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተወካዮች በተገኙበት በአዲስ አበባ ሃ/ስብከት አዳራሽ ታህሣሥ 14/2010 ዓ.ም […]

“እውነተኛው የዓለም ብርሃን”

ብርሃን ሁሉን የሚያሳይና ለፍጡራን ሁሉ የሚጠቅም የተፈጥሮ ፀጋ ስለሆነ መልካሙ ነገር ሁሉ በብርሃን ይመሰላል፡፡ ይሁን እንጂ ከስነ ፍጥረት የሚገኝ ብርሃን ተቃራኒ ስላለው ጊዜያዊ እንጂ ዘላቂና አስተማማኝ አይደለም፡፡ ለምሳሌ፡ – ከፀሐይ፣ ከጨረቃና ከክዋክብት እንዲሁም ከእሳት ወይም ከኤሌክትሪክና ከመሳሰሉ የተፈጥሮ ውጤቶች የሚገኝ ብርሃን ጊዜያዊ እንጂ ቋሚና አስተማማኝ ስላልሆነ አንድ ጊዜ ይበራል ሌላ ጊዜ ደግሞ ይጠፋል፡፡ ምክንያቱም የፀሐይ […]

የሚዘራና የሚያጭድ አብረው ደስ ይላቸዋል

ጠቢቡ ሰሎሞን “ለሁሉም ጊዜ አለው” ብሎ እንደተናገረው የዘርና የመከር ወቅቶች የተለያዩ ናቸው፡፡ በግብርና ሥራ ተመድበው የሚሠሩ ገበሬዎች በዘመነ ክረምት ይዘራሉ፡፡ በዘመነ መፀው ደግሞ በክረምት የዘሩትን ሰብል ያጭዳሉ፣ ይሰበስባሉ፣ ይከምራሉ፣ ይወቃሉ፡፡ ገለባውን ከፍሬው ለይተው በጎተራ ሲያከማቹ ገለባውን በእሳት ያቃጥላሉ በዚህም ሥራቸው ራሳቸውን ችለው በልተው፣ ጠግበው ለሌላውም ይተርፋሉ፡፡ የመዝሪያ የማጨጃና የመሰብሰቢያ ጊዜያት የተለያዩ እንደመሆናቸው መጠን የሠራተኞችም የዕለት […]

ስብከት

በመ/ር ሽፈራው እንደሻው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ከቀደምት አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንዷ እንደመሆኗ መጠን የተመሰረተችበት መሠረተ እምነት፤የተለያዩ ውሳኔዎችንና ሥርዓቶችን ያሳለፈችበትና የደነገገችበት ቀኖና እንዲሁም ከቀደሙት አባቶች የተረከበችው መንፈሳዊ ትውፊቷ  ምልከታዋን የሚያሰፉ  የማንነት መነጽሮቿ ናቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚሰጡ መንፈሳዊ አገልግሎቶች ተደራሽነታቸውን ለማስፋትና የአማንያኑን መንፈሳዊ ህይወት ለመገንባት በዓላትንና አፅዋማትን አስመርኩዞ ዘመኑን የሚዋጅና ወቅቱንም የሚዘክር አስተምህሮ በማዘጋጀት፤ተከታዮቿንም በመመገብና […]

beata2

የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ዓመታዊ በዓልና የገዳሙን መቶኛ ዓመት የምሥረታ በዓል በታላቅ ድምቀት አከበረ

በመ/ር ሣህሉ አድማሱ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓተ ቤተ መቅደስ በዓል እና የዳግማዊ አፄ ምኒልክን የዕረፍት መታሰቢያ በዓል በየዓመቱ ታህሳስ  3 ቀን ሲአከብር መቆየቱ ይታወቃል፡፡ በዘንድሮውም ዓመት ታህሳስ 3 ቀን 2010 ዓ.ም ባከበረው የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም በዓተ ቤተ መቅደስ  እና የዳግማዊ አፄ ምኒልክ የዕረፍት መታሰቢያ […]

መፃጉእ

በመ/ር ወንድምአገኝ ደጀኔ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የራሷ የሆነ ሥርዓተ አምልኮና ደንብ ያላት ቤተ-ክርስቲያን ናት፡፡ ሥርዓተ አምልኮዋን ከምትፈፅምባቸው መንፈሳዊ መሳሪያዎች መካከል አንዱ ፆም እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞ በአዋጅ ከደነገገቻቸው አፅዋማት መካከል አሁን እየፆምን የምንገኘው የነቢያት ፆም አንዱ ነው፡፡ ይህ ፆም ነቢያት የጌታን መወለድ በታላቅ ፍቅርና በጉጉት ሲጠባበቁ የፆሙት ፆም ነው፡፡ ሲጠበቅ የነበረውም የዓለም መድኃኒት […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት