የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መሠረተ ልማትና የአብነት ትምህርት ቤት!!April 1, 2016የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በ1996 ዓ.ም ታህሳስ ወር ላይ ተመሠረተ፡፡ በወቅቱ የአዲስ አበባ ከንቲባ በነበሩት በክቡር አቶ አርከበ እቁባይ ፈቃድ፣ ልዩ ትዕዛዝ፣ መመሪያ ሰጪነትና በአካባቢው ምዕመናን ርብርብ ተመሥርቷል፡፡ የቤተ ክርስቲያኑ አጠቃላይ የይዞታ ቦታ 54,444 ካሬ ሜትር ስፋት አለው፡፡ በዚህ ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ የሥራ ቦታ ተመድበው የሚሠሩ አገልጋዮች ብዛት 87 ናቸው፡፡ የደብሩ ዓመታዊ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/b22.jpg 425 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-04-01 13:16:392023-11-09 10:25:32የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መሠረተ ልማትና የአብነት ትምህርት ቤት!!
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስም በሐሰተኛ ሰነድ የተጠረጠሩ ግለሰዎች በህግ ቁጥጥር ሥር ዋሉMarch 30, 2016በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስም ሕገ ወጥ ማህተም፣ የመሥሪያ ቤቱ አርማና የዋና ሥራ አስኪያጁን የስም ቲተር አስመስሎ በመሥራት በሀገረ ስብከቱ ስም በሕገ ወጥ መንገድ ሠራተኞችን የቀጠሩና የተቀጠሩ እንዲሁም በመካከል አቀባባይ የሆኑ ደላሎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሀገረ ስብከቱም በደረሰው ጥቆማ መሠረት ለፖሊስ ባቀረበው ጥያቄ በዋና ሥራ አስኪያጁ ስምና ፊርማ እንዲሁም በሀገረ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/640.jpg 480 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-30 16:03:042023-11-09 10:25:32በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስም በሐሰተኛ ሰነድ የተጠረጠሩ ግለሰዎች በህግ ቁጥጥር ሥር ዋሉ
“ልትድን ትወዳለህን?”March 26, 2016በመምህር ሣህሉ አድማሱ በዐቢይ ጾም ከሚታሰቡት ሳምንታዊ ታሪኮች መካከል በአራተኛው ዕሑድ /ሰንበት/ የሚታሰበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ መጻጉዕ ይባላል፡፡ በዚህ ዕለት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በሌሊቱ አገልግሎት በዜማ የሚያሰሙት መዝሙር “አምላኩሰ ለአዳም” የሚለውን ያሬዳዊ ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ በጧቱ ሥርዓተ ቅዳሴ አገልግሎት ወቅት ደግሞ በዲያቆናቱና በቀሳውስቱ፣ በንባብና በዜማ የሚቀርቡት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መልእክቶች ወንጌልና የዳዊት መዝሙር ሲሆኑ እነዚህም (ገላ5÷1) […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png 0 0 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-26 13:51:572023-11-09 10:25:32“ልትድን ትወዳለህን?”
ጾም በክርስትና ሕይወትMarch 24, 2016የጾም ትርጉም ጾም፡-ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከጥሉላት ከሥጋ፣ከቅቤ፣ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ነው፡፡ከዚህም ሌላ ጾም ማለት፡- ዓይን ክፉ ከማየት ጆሮ ክፉ ከመስማት፣አንደበትክፉ ከመናገር፣እጅ ክፉ ከመሥራት በአጠቃላይ ሰውነት የኃጢአትሥራ ከመሥራት የሚገታበት፣ የሚከለከልበት ማለት ነው፡፡ጾም፡- ሁለት ዓይነት ነው ይኸውም ሀ.የግል ጾም ነው ፡-የግል ጾም ስንል አንድ ሰው በሠራው ኃጢአት ምክንያት ለንስሐ አባቱ ተናግሮ የሚሰጠው የንስሐ ጾም ሲሆን እንዲሁም አንድ ሰው ስለደረሰበትና በእርሱ ላይ ስለሆነ ነገር ስለሚፈልገው ጉዳይ እግዚአብሔር ተገቢውን መልስ እንዲሰጠው የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png 0 0 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-24 15:56:522023-11-09 10:25:32ጾም በክርስትና ሕይወት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 14ቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከግዕዝና ከአማርኛ ቋንቋዎች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀMarch 21, 2016 የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስራአራቱን ቅዳሴያት ከግዕዝና ከአማርኛ ቋንቋዎች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ በማስተርጎምና በማሳተም ቅዳሜ መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቀድሞ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዝደንት ዶ/ር ግርማ ወ/ጊዮርጊስ እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች በተገኙበት በኢሊሊ ሆቴል በይፋ ተመርቋል፡፡ ከአማርኛ እና ከግዕዝ ቋንቋዎች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ የተረጎመው አስራ አራቱ ቅዳሴያት በተመረቀበት ወቅት ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የቀሌም ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ወሊሶ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ላይ የተጻፈውን መነሻ በማድረግ በአማርኛ እና በኦሮምኛ ቋንቋዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የመግቢያ ንግግር አድርገዋል፡፡ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የወላይታ ዳውሮ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው በአስተላለፉት መልዕክት ለመወለድ፣ ለመሞት፣ ለመትከል፣ ለመንቀል ጊዜ አለው በማለት ጠቢቡ ሰሎሞን የተናገረውን ቃል መነሻ አድርገው ቋንቋ የመግባቢያ መሠረት መሆኑን፣ ቋንቋ እንደ መሸጋገሪያ ድልድይ አገልግሎት ያለው መሆኑን፣ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በአዲስ ኪዳን የተለያዩ ቋንቋዎች የነበሩ መሆናቸውን፣ ለሐዋርያት 72 ቋንቋዎችን መንፈስ ቅዱስ የገለጸላቸው መሆኑን እና ሰፊ ሕዝብ ሰፊ ቋንቋ ሊኖረው የሚገባ መሆኑን፣ አበባ የሚያምረው የተለያዩ ቀለማት ህብር ሲኖረው በመሆኑ፣ የምንለብሳቸው አልባሳት በተለያዩ ቀለማት የተዋቡ መሆናቸውን፣ ንብ የምትቀስመው አበባን ሲሆን በዚሁም ጣፋጭ ማር የምታስገኝ መሆኗን፣ ለአንድ መሠረታዊ ዓላማ ቋንቋ ወሳኝና አስፈላጊ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በርካታ መጻሕፍትን በየቋንቋው እያስተረጎመች የምትገኝ መሆኗን፣ የግዕዝ ቋንቋ የቤተ ክርስቲያን ብቸኛ ቅርስ በመሆኑ ተጠብቆ ሊኖር የሚገባው መሆኑን፣ ዛሬ ለምረቃ የበቃው አስራአራቱ ቅዳሴያት ብዙ ውጣ ውረድ እና ብዙ ድካም ያስከተለ ሲሆን ከዚህ በኋላ ግን ለውጤት የበቃ መሆኑን፣ ለዚሁም ሥራ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፣ ብፁዕ አቡነ ያሬድ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በኮሚቴነት ተመድበው ከፍተኛ አገልግሎት የሰጡ መሆናቸውን በማብራራት ሰፋ ያለ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/0159.jpg 425 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-21 13:22:312023-11-09 10:25:32በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 14ቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከግዕዝና ከአማርኛ ቋንቋዎች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀ
“የቤትህ ቅናት አቃጠለኝ”March 19, 2016በመምህር ሣህሉ አድማሱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አስተምሕሮ መሠረት በጾመ ኢየሱስ (ዐቢይ ጾም) ከሚከበሩት የሳምንታት በዓላት መካከል ሦስተኛው ሳምንት “ምኩራብ” በመባል ይታወቃል፡፡ የበዓሉ መታሰቢያ የሚታሰበው በዋናነት በዕለተ እሁድ ሲሆን በዚህ ዕለት በሌሊቱ ማሕሌታዊ ሥርዓት ወቅት “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ…” የሚል የቅዱስ ያሬድ ድርሰት በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በዜማ ይቀርባል፡፡ በሥርዓተ ቅዳሴው ወቅት ደግሞ ቆላ. […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png 0 0 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-19 14:32:212023-11-09 10:25:32“የቤትህ ቅናት አቃጠለኝ”
የጣሊያን ሪፐፕሊክ ፕሬዝዳንት ሰርጊዮ ማታሬላ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉMarch 14, 2016የተከበሩ ሚስተር ሰርጊዮ ማታሬላ የጣሊያን ሪፐፕሊክ ፕሬዝዳንት ሰኞ መጋቢት 5 ቀን 2008 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ተገኝተው ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጋር በአካባቢ ጥበቃ፣ በስደተኞች ጉዳይ እና በጋራ መልካም ግንኙነት ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት በ20ዎቹ ዓመታት ውስጥ የተደረገው […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/0062.jpg 425 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-14 15:45:002023-11-09 10:25:32የጣሊያን ሪፐፕሊክ ፕሬዝዳንት ሰርጊዮ ማታሬላ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ
የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የልማት እንቅስቃሴMarch 11, 2016የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ሥር የሚገኝ ሲሆን ይህ ቤ/ክ በ1986 ዓ.ም በአካባቢው ምዕመናን ተመሠረተ፡፡ የቤተክርስቲያኑ የይዞታ ቦታ 79,571 ካሬ ሜትር ስፋት አለው ሲሆን በቤተክርስቲያኑ በልዩ ልዩ የሥራ መስክ የተመደቡ ሠራተኞች ብዛት 93 ናቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያኑ እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በ3,310 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ፤ለአስራ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/g0021.jpg 425 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-11 14:44:092023-11-09 10:25:32የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የልማት እንቅስቃሴ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰባክያነ ወንጌል ፈተና ሰጠMarch 11, 2016የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከተ በስሩ ላሉት ገዳማትና አድባራት ሰባክያነ ወንጌል ለመመደብ ለመጀመሪያ ጊዜ ፈተና ሰጠ፡፡ ሀገረ ስብከቱ የመግቢያ ፈተናውን ያዘጋጀው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤና ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን በተውጣጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ለፈተናው ከተመዘገቡት አመልካቾች መካከልም በትምህርት ማስረጃቸው የተመረጡ 64 እጩዎች ለፈተና ተቀምጠዋል፡፡ በፈተናውም በዘመናዊ ትምህርት እስከ ማስተርስ ዲግሪ በመንፈሳዊም የአብነት ትምህርት ምሥክር የሆኑ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/640.jpg 480 640 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-11 14:10:552023-11-09 10:25:32የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰባክያነ ወንጌል ፈተና ሰጠ
አሥሩ ማዕረጋትMarch 11, 2016በመጋቢ አእላፍ ቀሲስ ፋሲል ታደሰ የቀበና ም/ፀሐይ መድኃኒዓለም ቤ/ክ/ስ/ወ/ኃላፊ ማዕረግ ማለት ክብር፣ ሥልጣን ማለት ነው፡፡ ቅዱሳን በገድልና በትሩፋት ብዛት የሚያገኟቸውን ዐሥር ማዕረጋትና ከዐሥር ቁጥር ጋር ያላቸውን ተያያዥነት እንመለከታለን፡፡ ቁጥር ምንድን ነው? በዕብራይስጥ ብዛትን ሲገልጥ ቁጥር በፊደል እንጂ በአኃዝ ምልክት ብዙ ጊዜ አልተጻፈም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ቁጥር አጠቃቀም ሌላ ነገር አለ፤ ይኸውም ቁጥሮች አንዳንድ ጊዜ የነገር፣ […] Read more https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png 0 0 tc https://eotc-aa.org/a/wp-content/uploads/logo_am-2.png tc2016-03-11 13:38:322023-11-09 10:25:32አሥሩ ማዕረጋት
የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መሠረተ ልማትና የአብነት ትምህርት ቤት!!
የቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን በ1996 ዓ.ም ታህሳስ ወር ላይ ተመሠረተ፡፡ በወቅቱ የአዲስ አበባ ከንቲባ በነበሩት በክቡር አቶ አርከበ እቁባይ ፈቃድ፣ ልዩ ትዕዛዝ፣ መመሪያ ሰጪነትና በአካባቢው ምዕመናን ርብርብ ተመሥርቷል፡፡ የቤተ ክርስቲያኑ አጠቃላይ የይዞታ ቦታ 54,444 ካሬ ሜትር ስፋት አለው፡፡ በዚህ ቤተ ክርስቲያን በልዩ ልዩ የሥራ ቦታ ተመድበው የሚሠሩ አገልጋዮች ብዛት 87 ናቸው፡፡ የደብሩ ዓመታዊ […]
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስም በሐሰተኛ ሰነድ የተጠረጠሩ ግለሰዎች በህግ ቁጥጥር ሥር ዋሉ
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ስም ሕገ ወጥ ማህተም፣ የመሥሪያ ቤቱ አርማና የዋና ሥራ አስኪያጁን የስም ቲተር አስመስሎ በመሥራት በሀገረ ስብከቱ ስም በሕገ ወጥ መንገድ ሠራተኞችን የቀጠሩና የተቀጠሩ እንዲሁም በመካከል አቀባባይ የሆኑ ደላሎች በቁጥጥር ሥር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሀገረ ስብከቱም በደረሰው ጥቆማ መሠረት ለፖሊስ ባቀረበው ጥያቄ በዋና ሥራ አስኪያጁ ስምና ፊርማ እንዲሁም በሀገረ […]
“ልትድን ትወዳለህን?”
በመምህር ሣህሉ አድማሱ በዐቢይ ጾም ከሚታሰቡት ሳምንታዊ ታሪኮች መካከል በአራተኛው ዕሑድ /ሰንበት/ የሚታሰበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ታሪክ መጻጉዕ ይባላል፡፡ በዚህ ዕለት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በሌሊቱ አገልግሎት በዜማ የሚያሰሙት መዝሙር “አምላኩሰ ለአዳም” የሚለውን ያሬዳዊ ቃለ እግዚአብሔር ነው፡፡ በጧቱ ሥርዓተ ቅዳሴ አገልግሎት ወቅት ደግሞ በዲያቆናቱና በቀሳውስቱ፣ በንባብና በዜማ የሚቀርቡት መጽሐፍ ቅዱሳዊ መልእክቶች ወንጌልና የዳዊት መዝሙር ሲሆኑ እነዚህም (ገላ5÷1) […]
ጾም በክርስትና ሕይወት
የጾም ትርጉም
ጾም፡-ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከጥሉላት ከሥጋ፣ከቅቤ፣ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ነው፡፡
ከዚህም ሌላ ጾም ማለት፡- ዓይን ክፉ ከማየት ጆሮ ክፉ ከመስማት፣አንደበትክፉ ከመናገር፣እጅ ክፉ ከመሥራት በአጠቃላይ ሰውነት የኃጢአትሥራ ከመሥራት የሚገታበት፣ የሚከለከልበት ማለት ነው፡፡
ጾም፡- ሁለት ዓይነት ነው ይኸውም
ሀ.የግል ጾም ነው ፡-የግል ጾም ስንል አንድ ሰው በሠራው ኃጢአት ምክንያት ለንስሐ አባቱ ተናግሮ የሚሰጠው የንስሐ ጾም ሲሆን እንዲሁም አንድ ሰው ስለደረሰበትና በእርሱ ላይ ስለሆነ ነገር ስለሚፈልገው ጉዳይ እግዚአብሔር ተገቢውን መልስ እንዲሰጠው የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን 14ቱ ሥርዓተ ቅዳሴ ከግዕዝና ከአማርኛ ቋንቋዎች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ ተተርጉሞ ተመረቀ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስራአራቱን ቅዳሴያት ከግዕዝና ከአማርኛ ቋንቋዎች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ በማስተርጎምና በማሳተም ቅዳሜ መጋቢት 10 ቀን 2008 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ ብፁዐን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የቀድሞ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፕሬዝደንት ዶ/ር ግርማ ወ/ጊዮርጊስ እና ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች በተገኙበት በኢሊሊ ሆቴል በይፋ ተመርቋል፡፡
ከአማርኛ እና ከግዕዝ ቋንቋዎች ወደ ኦሮምኛ ቋንቋ የተረጎመው አስራ አራቱ ቅዳሴያት በተመረቀበት ወቅት ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የቀሌም ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ወሊሶ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 2 ላይ የተጻፈውን መነሻ በማድረግ በአማርኛ እና በኦሮምኛ ቋንቋዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የመግቢያ ንግግር አድርገዋል፡፡
ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የወላይታ ዳውሮ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው በአስተላለፉት መልዕክት ለመወለድ፣ ለመሞት፣ ለመትከል፣ ለመንቀል ጊዜ አለው በማለት ጠቢቡ ሰሎሞን የተናገረውን ቃል መነሻ አድርገው ቋንቋ የመግባቢያ መሠረት መሆኑን፣ ቋንቋ እንደ መሸጋገሪያ ድልድይ አገልግሎት ያለው መሆኑን፣ በብሉይ ኪዳንም ሆነ በአዲስ ኪዳን የተለያዩ ቋንቋዎች የነበሩ መሆናቸውን፣ ለሐዋርያት 72 ቋንቋዎችን መንፈስ ቅዱስ የገለጸላቸው መሆኑን እና ሰፊ ሕዝብ ሰፊ ቋንቋ ሊኖረው የሚገባ መሆኑን፣ አበባ የሚያምረው የተለያዩ ቀለማት ህብር ሲኖረው በመሆኑ፣ የምንለብሳቸው አልባሳት በተለያዩ ቀለማት የተዋቡ መሆናቸውን፣ ንብ የምትቀስመው አበባን ሲሆን በዚሁም ጣፋጭ ማር የምታስገኝ መሆኗን፣ ለአንድ መሠረታዊ ዓላማ ቋንቋ ወሳኝና አስፈላጊ መሆኑን፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በርካታ መጻሕፍትን በየቋንቋው እያስተረጎመች የምትገኝ መሆኗን፣ የግዕዝ ቋንቋ የቤተ ክርስቲያን ብቸኛ ቅርስ በመሆኑ ተጠብቆ ሊኖር የሚገባው መሆኑን፣ ዛሬ ለምረቃ የበቃው አስራአራቱ ቅዳሴያት ብዙ ውጣ ውረድ እና ብዙ ድካም ያስከተለ ሲሆን ከዚህ በኋላ ግን ለውጤት የበቃ መሆኑን፣ ለዚሁም ሥራ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፣ ብፁዕ አቡነ ያሬድ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ በኮሚቴነት ተመድበው ከፍተኛ አገልግሎት የሰጡ መሆናቸውን በማብራራት ሰፋ ያለ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
“የቤትህ ቅናት አቃጠለኝ”
በመምህር ሣህሉ አድማሱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሥርዓተ አስተምሕሮ መሠረት በጾመ ኢየሱስ (ዐቢይ ጾም) ከሚከበሩት የሳምንታት በዓላት መካከል ሦስተኛው ሳምንት “ምኩራብ” በመባል ይታወቃል፡፡ የበዓሉ መታሰቢያ የሚታሰበው በዋናነት በዕለተ እሁድ ሲሆን በዚህ ዕለት በሌሊቱ ማሕሌታዊ ሥርዓት ወቅት “ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ…” የሚል የቅዱስ ያሬድ ድርሰት በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በዜማ ይቀርባል፡፡ በሥርዓተ ቅዳሴው ወቅት ደግሞ ቆላ. […]
የጣሊያን ሪፐፕሊክ ፕሬዝዳንት ሰርጊዮ ማታሬላ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ
የተከበሩ ሚስተር ሰርጊዮ ማታሬላ የጣሊያን ሪፐፕሊክ ፕሬዝዳንት ሰኞ መጋቢት 5 ቀን 2008 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ተገኝተው ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጋር በአካባቢ ጥበቃ፣ በስደተኞች ጉዳይ እና በጋራ መልካም ግንኙነት ዙሪያ ውይይት አድርገዋል፡፡ ፕሬዝደንቱ ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት በ20ዎቹ ዓመታት ውስጥ የተደረገው […]
የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የልማት እንቅስቃሴ
የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ሥር የሚገኝ ሲሆን ይህ ቤ/ክ በ1986 ዓ.ም በአካባቢው ምዕመናን ተመሠረተ፡፡ የቤተክርስቲያኑ የይዞታ ቦታ 79,571 ካሬ ሜትር ስፋት አለው ሲሆን በቤተክርስቲያኑ በልዩ ልዩ የሥራ መስክ የተመደቡ ሠራተኞች ብዛት 93 ናቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያኑ እየተሠሩ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በ3,310 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ግንባታ፤ለአስራ […]
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰባክያነ ወንጌል ፈተና ሰጠ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከተ በስሩ ላሉት ገዳማትና አድባራት ሰባክያነ ወንጌል ለመመደብ ለመጀመሪያ ጊዜ ፈተና ሰጠ፡፡ ሀገረ ስብከቱ የመግቢያ ፈተናውን ያዘጋጀው ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የሊቃውንት ጉባኤና ከአጥቢያ አብያተ ክርስቲያን በተውጣጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ነው፡፡ ለፈተናው ከተመዘገቡት አመልካቾች መካከልም በትምህርት ማስረጃቸው የተመረጡ 64 እጩዎች ለፈተና ተቀምጠዋል፡፡ በፈተናውም በዘመናዊ ትምህርት እስከ ማስተርስ ዲግሪ በመንፈሳዊም የአብነት ትምህርት ምሥክር የሆኑ […]
አሥሩ ማዕረጋት
በመጋቢ አእላፍ ቀሲስ ፋሲል ታደሰ የቀበና ም/ፀሐይ መድኃኒዓለም ቤ/ክ/ስ/ወ/ኃላፊ ማዕረግ ማለት ክብር፣ ሥልጣን ማለት ነው፡፡ ቅዱሳን በገድልና በትሩፋት ብዛት የሚያገኟቸውን ዐሥር ማዕረጋትና ከዐሥር ቁጥር ጋር ያላቸውን ተያያዥነት እንመለከታለን፡፡ ቁጥር ምንድን ነው? በዕብራይስጥ ብዛትን ሲገልጥ ቁጥር በፊደል እንጂ በአኃዝ ምልክት ብዙ ጊዜ አልተጻፈም፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ቁጥር አጠቃቀም ሌላ ነገር አለ፤ ይኸውም ቁጥሮች አንዳንድ ጊዜ የነገር፣ […]