• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የ2013 ዓ.ም የደመራ በዓለ መስቀል በመስቀል አደባባይ በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

በዓሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ የኢትዮጵያ ፕረዚዳንት ክብርት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ብፁአን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ክቡር መ/ሕይወት ቆሞስ አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪየጅ ፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ኃላፊዎች፣ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ክፍል […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስከያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ( ቆሞስ) የ2013 ዓ.ም በዓለ መስቀልን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!እንኳን ለ2013 ዓ.ም. ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ መስቀል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ !!! “የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት፥ ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔር ኃይል ነውና።”/1ቆሮ. 1፡18 / መስቀል በቤተ አይሁድ የርግማን ምልክት ፣ በቤተ አሕዛብ መራራ ቅጣት ፣ በቤተ ክርስቲያን ግን የድኅነት ሰሌዳ ነው ።ጌታችን ሞታችንን ወደ ሕይወት እንደ ለወጠ […]

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት ለህዳሴ ግድብ የ6 ሚሊዮን ብር ቦንድ ግዢ እንደሚፈጽም ገለጸ

በአራዳ ክፍለ ከተማ ለ10 ቀናት የቆየው የህዳሴ ግድብ ዋንጫ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ተባርኮ ወደ ሌላ ክፍለ ከተማ ተዛውሯል ለታላቁ ግድብ ግንባታ ገቢ ለማሰባሰብ እንደ ማነቃቂያ የሚጠቅመው የህዳሴው ግድብ ዋንጫ በአራዳ ክፍለ ከተማ ለ10 ቀናት ከቆየ በኋላ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ተባርኮ ወደ ሌላ ክፍለ […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስከያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ( ቆሞስ) የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

❖የተከበራችሁ የሀገረ ስብከታችን የዋና ክፍል እና የክፍል ሐላፊዎች እንዲሁም ሠራተኞች፣❖የተከበራችሁ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች እና ሠራተኞች፣❖ውድ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የሥራ ሓላፊዎችና ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣❖ የተወደዳችሁ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መላው ኦርቶዶክሳውያን የመንፈስ ልጆቻችን፣ እንኳን ከ2012 ዓ.ም. ዘመነ ዮሐንስ ወደ 2013 ዓ.ም. ዘመነ ማቴዎስ በሰላምና በጤና አሸጋገራችሁ ፣ አሸጋገረን ! ” ለከ ውእቱ መዓልት […]

የሀገረ ስብከቱ ጽ /ቤት ከከተማው አስተዳደር የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ /ቤት በ2012 ዓ. ም ላከናወናቸው በጎ የማኅበራዊ አገልግሎት ተግባራት የእውቅና ምስክር ወረቀት ከምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እጅ ተበርክቶለታል።ጳጉሜን 4 ቀን 2012 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሸራተን አዲስ ሆቴል ባዘጋጀው የምስጋና መርሐ ግብር ላይ የሀገረ […]

የ2013 አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእንኳን አደረሳችሁ መግለጫ ተሰጠ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2013 አዲሱን ዓመት አስመልክተው በሀገራችን በኢትዮጵያና በመላ ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵውያት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ቅዱስነታቸው የዘመናት ፈጣሪ የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ 2012 ዓ/ም ወደ ዘመነ ማቴዎስ 2013 ዓ/ም በሰላም አደረሳችሁ በማለት እግዚአብሔር መነሻም ሆነ፥ መገስገሻ […]

ርእሰ ዐውደ ዓመት የአዲስ ዘመን መጀመሪያ

በኢትዮጵያ ያለፈው ዓመት አልቆ የሚተካው የሚጀመርበት መስከረም አንድ ቀን ስለሆነ በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ርእሰ ዐውደ ዓመት ይባላል፡፡ ዘመን ሲያልፍ ዘመን ይተካል፡፡ ትውልድም ሲያልፍ ትውልድ ይተካል፡፡ ለኅልፈትና ለውላጤ የተፈጠረ ፍጡር ሁሉ ወቅትና ጊዜ አለው፡፡ በዚያው በተሰጠው ዘመን ሁሉም ሥራውን ያከናውናል አከናውኖም ያልፋል ያለሥራ የተፈጠረ ፍጡር የለምና፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረታትን ፈጥሮ ሲፈጽም “ወርእየ እግዚአብሔር ኵሎ ዘገብረ ከመ […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምእመናን ያሰባሰበችውን 40 ሚሊየን ብር በኦሮሚያ ክልል ጉዳት ለደረሰባቸው ምእመናን አከፋፈለች

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምሥራቅ ሐረርጌና የሱማሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የእርዳታ አሰባሳቢ ዐቢይ ኮሚቴ እና የጥናት ኮሚቴ በተገኙበት በዛሬው ዕለት ስለ ተገኘው ድጋፍና አከፋፈሉን በተመለከተ በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡የዐቢይ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ መኮንን ሰሙ በሰጡት መግለጫ በኦሮሚያ ክልል ለተጎዱት ምእመናን ዐቢይ ኮሚቴው ከተቋቋመበት ጊዜ […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደረሰባትን ወቅታዊ ችግር አስመልክቶ መግለጫ ሰጠች

ነሐሴ 20 ቀን 2012 ቅዱስ ፓትርያርኩ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ የጠ/ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብጹዕ አቡነ ያሬድ፣ በርካታ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ-ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች: የአ.አ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ፣ እንዲሁም በርካታ የሚዲያ ባለሙያዎችና እንግዶች በተገኙበት በቤተ ክርስቲያኒቱ እና ተከታይ ምእመናኖቿ ላይ እየደረሰ ስላለው ዘግናኝ ፍጅትና መከራ መግለጫ ሰጥታለች። በሀገራችን […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ 8ተኛ ዓመት መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ ለተቸገሩ ህጻናት እርዳታ ተሰጠ

ነሐሴ 10/2012 ዓ.ም በቅዱስነታቸው የመንፈስ ልጆቻቸው የተቋቋመው ፍቅረ ገብርኤል የወንድማማቾች ማኅበር በተባለ በጎ አድራጊ ማኅበር በካቴድራሉ ምግባረ ሠናይ ክፍል አስተባባሪነት በካቴድራሉ አካባቢ ለሚገኙ ተረጂ ህጻናት ለእያንዳንዳቸው 500 ብር፣ 10 ኪሎ ፍርኖ ዱቄት፣ 5 ሌትር ዘይት፣ 5 እሽግ ፓስታ፣ 5 ሳሙና 1 የትምህርት ቤት የተማሪዎች ቦርሳ፣ 1 ደርዘን ደብተር፣ 5 እስክሪብቶ፣ 3 ላጲስ፣ 3 እርሳስ መቅረጫ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት