• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ስብከተ ወንጌልን አስመልክቶ በሥሩ ከሚገኙት ከገዳማትና አድባራት ስብከተ ወንጌል ሐላፊዎች ጋር ሰፊ ውይይት አደረገ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ስብከተ ወንጌልን አስመልክቶ  በስሩ ከሚገኙት የገዳማትና አድባራት የስብከተ ወንጌል ሐላፊዎች ጋር ሰፊ የሆነ ውይይት ያደረገ ሲሆን በስብሰባው ላይ የአንድነት ጉባኤ፣ የስብከተወንጌል ኮሚቴ  የሚጠበቅበትን ሥራ ለምን አልሠራም፣ ሥልጠናን እንዴት እንስጥ የሚሉት ታላላቅና ወቅታዊ የሆኑ አጀንዳዎች ተነስተዋል፡፡ አጀንዳዎቹ ለታዳሚዎቹ በክፍለ ከተማው የስብከተ ወንጌል ሐላፊ በመጋቤ ሐዲስ ዘለዓለም […]

አዲሶቹ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የሥራ ሐላፊዎች ከገዳማቱና አድባራቱ ሐላፊዎች ጋር ትውውቅ አደረጉ

በአዲስ መልኩ የተመደቡት የጽሕፈት ቤቱ የሥራ ሐላፊዎች ከአንድ ሳምንት በፊት በሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ሐላፊዎችና የሥራ ባልደረቦች እንዲሁም በክፍላተ ከተሞች ሠራተኞች አቀባበል የተደረገላቸው ቢሆንም በቀን 11/2011 ዓ/ም ደግሞ ቅዱስ ፓትርያሪኩና ሌሎችም በርካታ ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ከአድባራቱና ገዳማቱ አስተዳደሪዎችና ጸሐፊዎች ጋር በሀገረ ስብከቱ የስብሰባ አዳራሽ የትውውቅ መርሐ ግብር ተደርጓል፡፡ በዚሁ የትውውቅ መርሐ ግብር ላይ መልእክታቸውን ያስተላለፉት […]

ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሥራ ሐላፊዎች ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያሪኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ሆነው የተመደቡት ብጹእ አቡነ መልከጼዴቅ እና በዋና ሥራ አስኪያጅነት የተመደቡት መ/ር አባ ሞገስ ኃይለ ማርያም በሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ሐላፊዎችና የሥራ ባልደረቦች እንዲሁም የክፍላተ ከተሞች ሥራ አስኪያጆችና ሠራተኞች በተገኙበት በሀገረ ስብከቱ የስብሰባ አዳራሽ ዛሬ የካቲት 2011ዓ/ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፡፡ በሀገረ ስብከቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የሥራ ሐላፊዎች ተመደቡለት

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክያን መንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤ/ክህነት መዋቅራዊ አስተዳደር ሥር ከሚገኙት አህጉረ ስብከቶች መካከል አንዱና አንጋፋው እንዲሁም የቅዱስ ፓትርያሪኩ ልዩ ሀገረ ስብከት የሆነው አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ነው፡፡ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ካሉበት ውስብስብና ዘርፈ ብዙ ችግሮች የተነሣ ብጥብጥና ትርምስ የማያጣው ተቋም እየሆነ ከመምጣቱም በላይ በርካታ የሥራ ሐላፊዎችን ያፈራረቀ ነው፡፡ በብጹእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ዘመነ ፕትርክና ብቻ […]

በዓለ አስተርእዮ

አስተርእዮ፡- ቃሉ ግእዝ ነው፡፡ አስተርእዮ ማለትም መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው፡፡
በግሪክ ቋንቋ ኤጲፋንያ ይባላል ኤጲፋንያ ማለት መገለጥ፤ መታየት ማለት ነው፡፡ አሁን ያለንበት ዘመን ዘመነ አስተርእዮ ይባላል የመገለጥ፣ የመታየት ዘመን ማለት ነው፡፡
ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነሥቶ ሰው ሆኖ የተገለጠበት ዘመን ስለሆነ እና እንዲሁም በጥምቀቱ አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠበት ዘመን …

ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዓለ ልደትን አስመልክተው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ

የ2011 ዓ/ ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደትን አስመልክቶ በርካታ ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳትና የሚድያ አካላት በተገኙበት በጽሕፈት ቤታቸው ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ። ጋዜጣዊ መግለጫውም “ሰላምን ሻት ተከተላትም” በሚል የመነሻ ሐሳብ የሰላም ዋጋ ምን ያክል ውድ እንደ ሆነና ሰላም ካልተጠበቀ በቀር ሊወሰድ የሚችል መለኮታዊ ስጦታ መሆኑንም ገልጸዋል። ከዝህም ጋር ተያይዞ ወቅታዊውን የሀገራችን የሰላም ችግርና የህዝብ እንግልት […]

ሰበር ዜና ሊቀ ጠበብት ኤልያስ ተጫነ ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሒሳብና በጀት ዋና ክፍል ሓላፊነት ተመለሱ

ከጠቅላይ ቤተ ክህነት በተላለፈ መመሪያ ወደሓላፊነታቸው የተመለሱት ሊቀ ጠበብቱ ቀደም ሲል የመደባቸው ቅዱስ ሲኖዶስ በመሆኑ የቅዱስ ሲኖዶስ ሉዓላዊ ስልጣን መከበር እንዳለበት ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የተላለፈው የእግድ ማንሻ ደብዳቤ ይገልጻል::ዝርዝር ዜናውን…..

መጋቤ ሃይማኖት ግርማይ ሐዲስ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሒሳብና በጀት ዋና ክፍል ሐላፊ ሆነው ተመደቡ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ሒሳብ ሹም ሆነው ሲሠሩ የቆዩት መጋቤ ሃይማኖት ግርማይ ሐዲስ በቁጥር 1984/0829//2011 በቀን 17/04/2011 ዓ.ም ከሀገረ ስብከቱ በተጻፈ ደብዳቤ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ሀገረ ስብከት በሆነው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በሒሳብና በጀት ዋና ክፍል ሃላፊነት ተመድበዋል፡፡

መጋቤ ሃይማኖት ግርማይ ሐዲስ በተለያዩ የቤተ ክርስቲያናችን የሥራ መስኮች በመንበረ ፖ/ቅ/ቅ/ማርያም፤በሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ፤በቦሌ ደ/ሳ/መድኃኔዓለምካቴድራልና በላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል አብያተ ክርስቲያናት በኃላፊነት እየተመደቡ ሲሠሩ የቆዩ ሲሆን በሠሩባቸው የሥራ ቦታዎች ሁሉ መልካም ስም እንዳላቸው ብዙዎች ይናገራሉ፡፡

የትምህርት ዝግጅታቸውን በተመለከተ በአካውንቲንግ የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ሲሆን በአሁን…..

ሥርዓተ ጸሎት

ጸሎት፡- ቃሉ ግእዝ ነው፡፡ ጸለየ ለመነ ከሚለው ግሥ የወጣ ሲሆን ጸሎት፡- ማለት ልመና ነው፡፡ ጸሎት ምስጋናም ነው “ይትቀደስ ስምከ” /ስምህ ይቀደስ/ ስንል ምስጋና ነው፡፡ “ሲሳየነ ዘለለዕለትነ ሀበነ ዮም” /የዕለት ምግባችንን ዛሬ ስጠን/ ስንል ደግሞ ልመና ነው፡፡ እንዲሁም ጸሎት፡- ሰው ከልዑል እግዚአብሔር ጋር የሚነጋገርበት ነው፡፡ /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 14/

በምን አይነት መንገድ መጸለይ እንዳለብን ከዚህ እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
በፍጹም እምነት መጸለይ ይገባል፡፡
በፍጹም እምነት የምንጸልየውን ጸሎት እግዚአብሔር ይቀበለዋል እየተጠራጠርን የምንጸልየውን ጸሎት ግን እግዚአብሔር አይቀበለውም፡፡ ጥርጥር ትልቅ የሰው ባለጋራ /ጠላት/ ነው፡፡ ጥርጥርን ማስወገድ ያስፈልጋል “አምናችሁ በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ” /ማቴ. 21፡22/

በቅን ልቡና፣ በንጹሕ ልብ መጸለይ ይገባል
በቅን ልቡና፣ በንጹሕ ልብ የምንጸልየውን ጸሎት እግዚአብሔር ይቀበለዋል፡፡ ልባችንን የቂም በቀልና የክፋት ምሽግ አድርገን የምንጸልየውን ጸሎት ግን እግዚአብሔር አይቀበለውም፡፡ “ጸሎቱ ለመስተቀይም ከመዘርዕ ዘወድቀ ማእከለ አሥዋክ” /የቂመኛ ሰው ጸሎት …..

ጾም በክርስትና ሕይወት

በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን
1.የጾም ትርጉም
2. ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
3. የጾም ጥቅሞች
4. በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡
ከላይ ከ1-4 ተራ ቍጥር የተገለጹትን እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን…

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን