• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መጠናቀቁን አስመልክቶ ባለ 15 ነጥብ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጠ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ሕገ ቤተ ክርስቲያንንና ኦርቶዶክሳዊ ቀኖናውን መሠረት ባደረገ መልኩ በዓመት ሁለት ጊዜ ማለትም በጥቅምትና በግንቦት ወር የሚካሄድና በቅዱስ ፓትርያሪኩ የሚመራ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወይም ስብሰባ ታደርጋለች፡፡    የርክበ ካህናት መምጣትን ተከትሎ በግንቦት ወር የሚደረገው ሁለተኛው የብፁዓን አባቶች የሲኖዶስ ምልዓት ጉባኤ  ወይም ስብሰባ ግንቦት 13 ቀን /2011 ዓ/ም  በጸሎት […]

“ይኩንኪ በከመ ተአመንኪ” /እንዳመንሽ ይሁንልሽ/ /ማቴ. 15፡28/

ይህ ቃል ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለከነናዊት ሴት የተናገረው ቃል ነው፡፡ ታሪኩም /በማቴዎስ ወንጌል ም.15፡21-28/ ላይ ይገኛል፡፡ ታሪኩም እንደሚከተለው ተገልጻ_ል፡፡         “ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ፡፡ በዚያም ከነናዊት ሴት ጌታ ሆይ! የዳዊት ልጅ ማረኝ ልጄን ጋኔን ክፉኝ ይዟታል ብላ ጮኸች፡፡ እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም፡፡ ደቀመዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው በኋላችን […]

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ የ2011 ዓ.ም የትንሣኤ በዓልን አስመልክተው መልእክት አስተላለፉ

ሙሉ የቅዱስነታቸው መልእክት እንደሚከተለው ይቀርባል ቃለ በረከት ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ዘተናገረ በበዐለ ትንሣኤሁ ለእግዚእነ ወአምላክነ ወመድኃኒነ ኢየሱስ ክርስቶስ በዕሥራ ምእት ዐሠርቱ ወአሐዱ ዓመተ ምሕረት በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤ ከሀገር ውጭ […]

006

“ሕያዉን ከሙታን ጋር ለምን ትፈልጉታላችሁ? በዚህ የለም ተነሥቷል” /ሉቃ. ፳፬፡፭/

ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን እንደሚነሣ ቅዱሳን ነቢያት አስቀድመው ትንቢት ተናግረዋል፡፡ ከትንቢቶቹም አንዱ “ወተንሥአ እግዚአብሔር ከመ ዘንቃሕ እምንዋም፡፡ ወከመ ኃያል ወኅዳገ ወይን፡፡ ወቀተለ ጸሮ በድኅሬሁ” /የተኛ ሰው ከእንቅልፍ እንደሚነቃ እግዚአብሔር ከሙታን ተነሣ የወይን ስካር እንደተወው እንደ ኃያልም ሰው፤ በኋላው በተተከለ መስቀል ጠላቱን ድል አደረገ/ /መዝ. 77፡65/       ስለ ጌታችን ትንሣኤ አራቱም ወንጌላውያን ጽፈዋል፡፡ ይህም /ማቴ. […]

002

በዓለ ሆሣዕና

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆሣዕና በዓል ነው፡፡ ስለዚህ በዓል አስቀድሞ ትንቢት ተነግሯል፤ ከትንቢቶቹም አንዱ እንደሚከተለው ተጠቅሷል፡፡ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በይ እነሆ ንጉሥሽ ትሑት ሆኖ በአህያና በአህያይቱ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል” /ትን. ዘካ. 9፡9/ ከዚህም ጋር ስለበዓለ ሆሣዕና አራቱም […]

‹‹ጥንተ ስቅለት››

የዓለም መድኅን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም በነሣው ሥጋ በቀራንዮ መስቀል ላይ ተሰቅሎ ሕይወቱን ለዓለም ቤዛ፣ አድርጎ የሰጠው መጋቢት ፳፯ ቀን ፴፫ ዓ.ም እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህ ቀን ስለክርስቶስ ሕማም፣ ስለመከራ መስቀሉና ስለሞቱ የተነገሩት ትንቢቶችና ምሳሌዎች ሁሉ የተፈጸሙበት፤ ሰማያዊ አምላክ ስለሰው ልጆች ፍቅር ሲል ልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራዎችን የተቀበለበትና በሞቱ ሞትን ሽሮ የአዳምን ዘር ሁሉ […]

መልካም ባልንጀራ

ምስጢር የሚያወያዩትን አብሮ የሚሠሩትንና ጧት ማታ የሚገናኙትን እንዲሁም አብሮ አደግየሆነውን ሰው ባልንጀራዬ ነው ብሎ መናገር የተለመደ ነው፡፡ ዛሬ ለኔ ነገ ላንተ እየተባባሉ አብረው ከሚውሉት፣ ከሚያመሹት ጓደኞቻቸው ሌላ ባልንጀራ ያለ የማይመስላቸውም ብዙዎች ናቸው፡፡ በመሠረቱ አብሮ መብላትና መጠጣት ወይም በአንድ ላይ ተምሮ ማደግና አብሮ መኖር ይልቁንም ትንሽ ትልቁን ክፉና ደጉን ምስጢር መካፈል ባልንጀራ ሊያሰኝ ቢችልም ይህ ብቻ […]

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ፮ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በደማቅ ሁኔታ ተከበረ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፬ኛ ፓትርያርክ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ ከ34 በላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የእስልምና ዋና ሐላፊ ሸክ አህመድ፣ የቤተክህነት ሠራቶኞች፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ በርከት ያሉ ምእመናንና እንግዶች በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ […]

ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የዓብይ ጾም መግባትን አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጡ

በቤተክርስቲያንችን ቀኖናዊ ሥርዓተ እምነት መሠረት በጾምና በጸሎት ከምንዘክራቸውና ፈቃደ ሥጋችንን ለፈቃደ ነፍሳችን ከምናስገዛበቸው አጽዋማት መካከል ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾሞ በአርዓያነት ያሳየን ጾመ ኢየሱስ ወይም ዓብይ ጾም አንዱ ነው፡፡ በዚሁ የገዳመ ቆሮንቶስ ጾም ወቅት የሰውን ልብ በእጅጉ የሚገዳደሩና ለውድቀትም የሚዳርጉ የኃጢአትና የበደል ምክንያቶች ሁሉ በክርስቶስ ባሕሪያዊ ገንዘብ በሆነው በኃይሉ ችሎት ከመንገዳቸው ወጥተዋል የሰይጣንም ሽንፈት ተረጋግጧል፡፡ […]

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት የክፍል ኃላፊዎች የስድስት ወር ሪፖርት አዳመጠ

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራአስኪያጅ ቆሞስ አባ ሞገስ ኃ/ማርያም ፣ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበብ ምናሴ ወ/ሐና፣ የየክፍሉ ኃላፊዎች፣ የሀ/ስብከቱና የሰባቱ ክፍለ ከተሞች ሠራተኞች በተገኙበት በሀ/ስብከቱ የስብሰባ አዳራሽ የሁሉም ክፍል ኃላፊዎች የስድስት ወር ሪፖርት ቀርቧል። በሪፖርቱ ብዙ አመርቂ የሚባሉ ሥራዎች እንዳሉ ሆነው በአንጻሩ ደግሞ ብዙ ሊሠሩ የሚገባቸው ሳይሠሩ እንደቀሩና ለወደፊቱ ትኩረት ተሰጥቶባቸው በአግባቡና በጊዜው […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን