• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በዋና ሥራ አስኪያጅነት የተመደቡት 27ኛው ተሿሚ መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ በሀገረ ስበከቱ የስብሰባ አዳራሽ ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ጽ/ቤት በሀገሪቱ ርእሰ መዲና አዲስ አበባ ከተመሠረተ ጀምሮ የበርካታ ሥራ አስኪያጆችን ታሪካዊ አሻራ አስተናግዶ አሁን ደግሞ መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃ/ገብርኤል ነገሽን 27ኛው የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ አድርጎ ሾሟል። ላለፉት 12 ወራት ጽ/ቤቱን በዋና ሥራ አስኪያጅነት ሲመሩት የነበሩት መልአከ ሕይወት አባ ሞገስ ኃ/ማርያም የካቲት 20/2012 ዓ/ም ተሰናብተው በምትካቸው ደግሞ የምስራቀ ፀሐይ ቅዱስ […]

መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኀይለ ገብርኤል ነጋሽ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ተመደቡ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ወአቡነ አዳም ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ የነበሩት መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኀይለ ገብርኤል ነጋሽ በቁጥር 3136/2012 በቀን 20/06/2012 ዓ.ም ከጠቅላይ ቤተ ክህነት በተጻፈ ደብዳቤ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ሀገረ ስብከት በሆነው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በዋና ሥራ አስኪያጅነት ተመድበዋል፡፡ ለዋና […]

ጾም በክርስትና ሕይወት

በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን የጾም ትርጉም ጾም ያስፈለገበት ምክንያት የጾም ጥቅሞች በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡ ከላይ ከ1-4 ተራ ቊጥር የተገለጹትን እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡ 1ኛ/ የጾም ትርጉም ጾም፡- ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ማለት ሲሆን ከሥጋ፣ ከቅቤና፣ ከእንቁላል ደግሞ እንድንጾምባቸው የተወሰኑ የአጽዋማት ሳምንታት እስኪጠናቀቁ […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አደረገች

“በጎውን ማን ያሳየናል” በሚል መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል መነሻነት ወቅታዊና አንገብጋቢ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ መምህራነ ቤተክርሰቲያን፣ የዘርፉ ምሁራን ፣የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በጎልደን ቱሊፕ ሆቴል ሰፊ ምክክርና ውይይት ተከናውኗል፡፡መርሐ ግብሩ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ […]

በጸጥታ አካላት በተተኮሰ ጥይት የተገደሉት ሁለት ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶች ሥርዐተ ቀብር ተፈጸመ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት በቦሌ ክፍለ ከተማ ሥር በሃያ ሁለት አካባቢ ቀበሌ ሃያ አራት ልዩ ስሙ አፍሮ ጽዮን አዋሳኝ በሚባለው ባዶ ሥፍራ ዙሪያ ለሚገኙት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ተከታይ ምዕመናን ይሆን ዘንድ የአምልኮ ሥፍራ ማለትም ቤተ-ክርስቲያን ለመስራት በአካባቢው ምዕመናን ትብብር ጊዜያዊ መጠለያ ሠርተው በተቀመጡት አማንያንና ቦታው ለአረንጓዴ ልማት የተከለለ ነው በሚሉ የጸጥታ አካላት መካከል […]

በዓለ አስተርእዮ

አስተርእዮ፡– ቃሉ ግእዝ ነው፡፡ አስተርእዮ ማለትም መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው፡፡ በግሪክ ቋንቋ ኤጲፋንያ ይባላል ኤጲፋንያ ማለት መገለጥ፤ መታየት ማለት ነው፡፡ አሁን ያለንበት ዘመን ዘመነ አስተርእዮ ይባላል የመገለጥ፣ የመታየት ዘመን ማለት ነው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነሥቶ ሰው ሆኖ የተገለጠበት ዘመን ስለሆነ እና እንዲሁም በጥምቀቱ አንድነቱን ሦስትነቱን […]

የኦርቶዶክሳዊ አገልግሎታችን ልዕልና እንመልስ በሚል ርእስ የጽሁፍ ዳሰሳ ቀረበ

በዛሬ ዕለት በአዲስ አበባ ሀ/ስብከት አዳራሽ፣ የሀ/ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣  የሀ/ስብከቱ ስብከተ ወንጌል ዋና ክፍል ኃላፊ፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሐዋርያዊ ተልእኮና ስብከተ ወንጌል መምሪያ ምክትል ኃላፊ፣ የሀገረ ስብከቱ ክፍል ኃላፊዎች፣ የየካና ቦሌ ክፍላተ ከተማ አስተዳዳሪዎች፣ ስብከተ ወንጌል ኃላፊዎችና ሰባክያን በተገኙበት በመ/ር ግርማ ባቱ የተዘጋጀ የኦርቶዶክሳዊ አገልግሎታችን ልዕልና እንመልስ በሚል ርእስ የጽሁፍ ዳሰሳ ቀርበዋል። በዝግጅቱ በአገልግሎታችን […]

የሚዘራና የሚያጭድ አብረው ደስ ይላቸዋል

ጠቢቡ ሰሎሞን “ለሁሉም ጊዜ አለው” ብሎ እንደተናገረው የዘርና የመከር ወቅቶች የተለያዩ ናቸው፡፡ በግብርና ሥራ ተመድበው የሚሠሩ ገበሬዎች በዘመነ ክረምት ይዘራሉ፡፡ በዘመነ መፀው ደግሞ በክረምት የዘሩትን ሰብል ያጭዳሉ፣ ይሰበስባሉ፣ ይከምራሉ፣ ይወቃሉ፡፡ ገለባውን ከፍሬው ለይተው በጎተራ ያከማቻሉ በዚህም ሥራቸው ራሳቸውን ችለው በልተው፣ ጠግበው ለሌላውም ይተርፋሉ፡፡ የመዝሪያ የማጨጃና የመሰብሰቢያ ጊዜያት የተለያዩ እንደመሆናቸው መጠን የሠራተኞችም የዕለት ኑሮ የተለያየ ሁኔታ […]

ቅዱስ ሲኖዶስ በሀገራችን ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የአቋም መግለጫ ሰጠ

በዓመት ለሁለት ጊዜ ከሚካሄዱት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤያት መካከል አንዱ መደበኛውን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤተከትሎ የሚደረገው የጥቅምት ምልዓተ ጉባኤ ነው፡፡ይህንን ጉባኤ አስመልክቶም ትናንት ጥቅምት 12 ቀን የመክፈቻ መግለጫውን መስጠቱም ይታወቃል፡፡በዛሬው ዕለት ደግሞ ማለትም ጥቅምት 13/2012 ዓ/ምሁሉም የምልዓተ ጉባኤው አባላትና በርካታ የሚዲያ ባለሙያዎች በተገኙበት ለመወያያ ከቀረቡት አጀንዳዎች መካከል የሀገርን ጉዳይ ቅድሚያ በመስጠት የሰላም ጥሪ ለማድረግ መገደዱን በመግለጫው […]

ዓመታዊው የወርኃ ጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ተጀመረ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ዓመታዊው የወርኃ ጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በቀን 12/2012 ዓ.ም በብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የመግለጫ ንግግር ተጀመረ፡፡ በምልአተ ጉባኤው የመክፈቻው ንግግር ላይ የቤተክርሰቲያኗ፤የመንግሥትና የግል ሚዲያዎች ተገኝተው የዘገቡ ሲሆን ፓትርያርኩም ወቅታዊ የሆኑትን የቤተክርስቲያኗን ተግዳሮቶች በመጥቀስ ከምልአተ ጉባኤው ምን እንደሚጠበቅ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን