• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ሐምሌ 18 ቀን በምዕራፈ ሰማዕት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን የቡራኬ ሥነ ሥርዓት ላይ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ያስተላለፉት መልእክት

“በለሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል፡፡” ምሳ. 27፡18 ብጹዕ አባታችን አቡነ ፊሊጶስየተከበራችሁ በዚህ የተሰበሰባችሁ ምእመናን እና ምእመናት የሁሉ ፈጣሪ፣ የሁሉ መጋቢ የሆነው አምላካችን፤ በዚህ በኀዘንና በጭንቀት ወቅት የምንጽናናበት፣ ቃሉን የምንሰማበትን ቅዱስ ቤቱን እንድናከብር ስለፈቀደልን ክብርና ምሥጋና ለእርሱ ይሁን!!እንኳን ደስ አለን!!!እንኳን ደስ አላችሁ!!! ጠቢቡ ንጉሥ ሰሎሞን እግዚአብሔርን ደጅ በመጥናት፣ ትእግስትን ገንዘብ በማድረግ የሚገኘውን ልዩ ጸጋ በምሳሌ ሲገልጽልን “በለሱን […]

በቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶ ሃያ አራት ተብሎ በሚጠራው አከባቢ ተገንብቶ የተጠናቀቀው የቅዱስ ገብርኤልና የቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን ተመረቀ

እጅግ በሚያስደንቅ ሁኔታ በፍጥነት ተሠርቶ ያለቀው ይህ ቤተክርስቲያን ብፁእ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ የበላይ ጠባቂ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ቆሞስ አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት ሠራተኞች፣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የየክፍሉ ኃላፊዎች፣የቦሌ ክፍለ ከተማ ሠራተኞች፣ካህናትና ዲያቆናት፣የሰንበት ትምህርት ቤት አባላትና የአከባቢው ምእመናን […]

የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ በችግኝ ተከላና ክብካቤ ዙሪያ የቀረበለትን ጥናት ተወያይቶ አጸደቀ

የሀገረ ስብከቱ አስተዳደር ጉባኤ በችግኝ ተከላና ክብከቤ ፕሮጀክት ዙሪያ ተወያይቶ ተግባራዊ እንዲሆን ወሰነ፡፡ በሀገረ ስብከቱ ዕቅድና ልማት ዋና ክፍል በኩል በተጋበዙ ባለሙያ ተዘጋጅቶ የቀረበው “የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የችግኝ ተከላ እና ክብካቤ ፕሮጀክት” በከተማችን ባሉ ገዳማትና አድባራት የነበረው ዐጸደ ቤተ ክርስቲያን ሽፋን በልማትና በተለያዩ ግንባታዎች እየተመናመነ በመምጣቱ የደን ሽፋኑን ወደ ነበረበት ሁኔታ ለመመለስ ያለመ ነው፡፡በባለሙያ […]

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ በሚሊኒየም ፓርክ ችግኝ ተከሉ

ሰኔ 10 ቀን 2012 የአ.አ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽና የዋና ክፍል ኃላፊዎች ፣የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋም ጉባኤ አባላት፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳድር ም/ከንቲባ ተወካይና የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ ፣ እንዲሁም የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሠራተኞችና በርካታ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት በየካ ተራራ ላይ በሚገኘው ሚሊኒየም ፓርክ የችግኝ ተከላ ተካሂዷል። […]

“ይኩንኪ በከመ ተአመንኪ” /እንዳመንሽ ይሁንልሽ/ ማቴ.15፥28

ይህ ቃል ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለከነናዊት ሴት የተናገረው ቃል ነው፡፡ ታሪኩም /በማቴዎስ ወንጌል ም.15፡21-28/ ላይ ይገኛል፡፡ ታሪኩም እንደሚከተለው ተገልጻል፡፡“ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ጢሮስና ወደ ሲዶና አገር ሄደ፡፡ በዚያም ከነናዊት ሴት ጌታ ሆይ! የዳዊት ልጅ ማረኝ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዟታል ብላ ጮኸች፡፡ እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም፡፡ ደቀመዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው በኋላችን ትጮኻለችና […]

ለአዲስ አበባ ሀገረ ሰብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ ከአሁን በፊት በሚያስተዳድሩበት ደብር ደማቅ የሽኝት መርሐ ግብር ተደረገላቸው

ሰኔ 7 ቀን 2012 የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ፤ የነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ትፍሥት ግርማ እና ሠራተኞች፤ የደብሩ ማኅበረ ካህናትና የደብሩ ሰ/ት/ቤት ወጣቶች እንዲሁም በርካታ የአካባቢው ማኅበረ ምእመናን በተገኙበት በጀሞ ምሥራቀ ጸሐይ ቅ/ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በቃለ እግዚአብሔር የታጀበ […]

የ2012 ዓ/ም ዓመታዊ የፐርሰንት አሰባሰብን አስመልከቶ ውይይት ተካሄደ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የስብሰባ አዳራሽ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ፤ የሀገረ ስብከቱ የየዋና ክፍል ኃላፊዎች፤የሁሉም ክፍላተ ከተሞች ሥራ አስኪያጆችና ሠራተኞች እንዲሁም የአድባራትና ገዳማቱ አስተዳዳሪዎች፤ ሊቃነ መናብርትና ሒሳብ ሹሞች በተገኙበት ዓመታዊ የፐርሰንት ገቢ ካላጠናቀቁ አድባራትና ገዳማት ጋር ውይይት ሰኔ 4/2012 ዓ/ም ተደርጓል፡፡ወቅታዊውን የኮረና ወረርሽኝ ለመከላከል ሲባል የውይይት መርሐ ግብሩ […]

ጾመ-ሐዋርያት

“ቀድሱ ጾመ ወስብኩ ምሕላ ጾምን ለዩ ምሕላንም አውጁ“ (ኢዮ 1÷14)ጾም የሚለው ቃል “ጾመ“ ተወ ፤ታቀበ፤ ታረመ ከሚለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ጥቅል ትርጉሙም ጥሉላትን መባልዕትን ፈጽሞ መተው መከልከልና መወሰን ወይም ደግሞ ሰውነትን ከሚያምረውና ከሚያስጎመጀው መብልና መጠጥ እንዲሁም ከክፉ ነገር ሁሉ ራስን መጠበቅ መቆጣጠርና መግዛት ማለት ነው፡፡ ጾም የመላ ሰውነታችንን መታዘዝ የሚጠይቅ መንፈሳዊ ተግባር እንጅ በተወሰኑ […]

በአዲስ መልክ የተሠራው የጉራራ ኪዳነ ምሕረት ህንጻ ቤተ ክርስቲያን ተመረቀ

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሚገኘው የጉራራ ምስራቀ ፀሀይ ቅድስት ኪዳነ ምህረት እና የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ግንቦት 29/2012ዓ.ም ቅዳሴ ቤቱ ተፈጽሞ ተመርቋል። በምረቃው ሥነስርዓት ላይ የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከተ ሊቀ ጳጳሰ ብፀዕ አቡነ እንጦስ ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስኪያጅ መልአከ ህይወት አባ ኃይል ገብርኤል ነጋሽ ፣ የደብሩ […]

የ2012 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ መርሐ ግብር ተካሄደ

ግንቦት 28/2012 ዓ.ም ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፤ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ፤ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃይለ ገብርኤል ነጋሽ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ስራ አስከያጅ እና የሐይማኖት ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት የችግኝ ተከላ መርሐ ግብሩ ተካሂዷል፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን