• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የዛሬው የ39ኛው የሰበካ ጉባኤ ስልጠና በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት አስተባባሪነት በሳሪስ ም/ቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤ/ክ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተካሄደ

በዛሬው ዕለት መጋቢት 14 ቀን 2013 ዓ.ም የመ/ፓ/ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ላዕከ ሰላም ቀሲስ ሰሎሞን ቶልቻ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ብርሃን ሳሙኤል ደምሴ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰ፣ የሀገረ ስብከቱና የክፍለ ከተማው የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በአቃቂ […]

የሙዳይ በጎ አድራጎት ማኅበር ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የምስጋና ምስክር ወረቀት አበረከተ

የሙዳይ በጎ አድራጎት ማኅበር በአሁኑ ሰዓት 450 ሴቶችንና 650 ሕጻናትን የሚንከባከብና የሚያስተምር የበጎ አድራጎት ማኅበር ነው።የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ይህንን በእግዚአብሔርም ሆነ በሰው ፊት መልካም የሆነውን የማኅበሩን ሥራ ለማበረታታትና የድርሻውን ለመወጣት በሀገረ ስብከቱ ምግባረ ሰናይ ዋና ክፍል አስተባባሪነት የተሰበሰቡ የትምህርት ቁሳቁሶችንና የተለያዩ አልባሳትን ከአንድም ሁለት ጊዜ ለማኅበሩ ድጋፍ ማድረጉ የሚታወስ ነው።የሙዳይ በጎ አድራጎት ማኅበርም […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያበረከተችው አስተዋጽኦ የማይተካ ሚና እንዳለው በ39ኛው የሰበካ ጉባኤ ስልጠና ላይ ተገለጸ!!

መጋቢት 13 ቀን 2013 ዓ.ም የመ/ፓ/ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ኃላፊ ላዕከ ሰላም ቀሲስ ሰሎሞን ቶልቻ፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ብርሃን ሳሙኤል ደምሴ፡የአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ሃይማኖት ጸጋዬ ገ/ዮሐንስ፡ የሀገረ ስብከቱና የክፍለ ከተማው የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም በአራዳና ጉለሌ ክፍለ ከተማ ሥር […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በተዘጋጀው ዐውደ ወንጌል ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጉባኤ ተገኝተው ትምህርተ ወንጌልና ቃለ ምዕዳን ሰጡ

የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳሰ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በመካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል በተዘጋጀው ዐውደ ወንጌል ዘኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጉባኤ ተገኝተው ትምህርተ ወንጌልና ቃለ ምዕዳን ሰጥተዋል።በጉባኤው ክቡር መ/ር አካለወልድ ተሰማ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፥ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፈ የሀገረ ሰብከቱ የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ፥ ሊቀ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅና መ/ር አካለወልድ ተሰማ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ትምህርተ ወንጌልና የሥራ መመሪያ ሰጡ

የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳሰ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅና የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ር አካለወልድ ተሰማ በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ትምህርተ ወንጌልና የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።በቦታው ክቡር አባ ወልደኢየሱስ ሰይፈ የሀገረ ሰብከቱ የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ፥ ክብር መልአከ ሣህል ቆሞስ አባ ተክለ ብርሃን ደስታ የደብሩ አስተዳዳሪ፥ የደብሩ ካህናት […]

ጎተራ አካባቢ የሚገኘው ጥንታዊው የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ሕንጻ ቤ/ክ እድሳት ሊካሄድለት ነው

በዛሬው ዕለት መጋቢት 11 ቀን 2013 ዓ/ም የጉራጌ እና የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፈ፣ የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ-ክርስቲያን አስተዳደሪ መልአከ ፀሐይ ተስፋ ማርያም ነጋሽ፣ የደብሩ ማኅበረ ካህናት እና የደብሩ የሰ/ት/ቤት መዘምራን ወጣቶች እንዲሁም በርካታ ምዕመናን […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲሱ የሀገረ ስብከቱ አሰራርን አስመልክተው ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉት ቀለ መጠይቅ

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲሱ የሀገረ ስብከቱ አሰራርን አስመልክተው ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ያደረጉትን ቀለ መጠይቅ ይመልከቱ ሌሎችም እንዲያዩት በፌስ ቡክ፣ በቴሌግራም፣ በዩቲዩብ….. ሼር ያድርጉ!!!

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የዐብይ ጾም መግቢያን አስመልክተው ያስተላለፉት አባታዊ መልእክት

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የዐብይ ጾም መግቢያን አስመልክተው አባታዊ መልእክት አስተላለፉ

ብፁዕነታቸው እንደገለጹት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከደነገገቻቸው አጽዋማት መካከል አንዱ የዐቢይ ጾም ነው ፤ ዐቢይ የሚለው ቃል ትርጉሙ ትልቅ ማለት ሲሆን የጾሙን ታላቅነት ይገልጻል፤ ዐቢይ ጾም የተባለበት ምክንያት ጌታችን አምላካችን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ስለጾመውና ለተከታታይ ስምንት ሳምንታት ሳይቋረጥ የሚጾም ጾም በመሆኑ ነው፤ በእያንዳንዱ ሳምንት ውስጥ ያሉት እሑዶች የየራሳቸው የሆነ ስያሜ፣ ትርጉምና ልዩ ምሥጢር እንዳላቸው […]

የሀገረ ስብከቱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አጠቃቀም ትግበራ

“እንግዲህ እንደ ጥበበኞች እንጂ ጥበብ እንደሌላቸው ሳይሆን እንዴት እንድትመላለሱ በጥንቃቄ ተጠበቁ፤ ቀኖቹ ክፍዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ”፡፡ ኤፌ. 5÷15 በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ አሁን የምንገኝበት ዘመን የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጥቅም ጎልቶ የታየበት ዘመን በመሆኑ በዚሁ ቴክኖሎጂ ኦቶሜሽን ሲስተም ያልታገዘ አሠራር አዝጋሚ እና አድካሚ ከመሆኑም በላይ ብክነትን ባስወገደ መልኩ የሚፈለገውን ያህል  አጥጋቢ እና ውጤታማ ለመሆን ያስቸግራል። ሀገረ ስብከቱ በሥሩ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት