• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የሀገረ ስብከቱ ጽ /ቤት ከከተማው አስተዳደር የዕውቅና ሽልማት ተበረከተለት

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ /ቤት በ2012 ዓ. ም ላከናወናቸው በጎ የማኅበራዊ አገልግሎት ተግባራት የእውቅና ምስክር ወረቀት ከምክትል ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ደመቀ መኮንን እና የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ እጅ ተበርክቶለታል።ጳጉሜን 4 ቀን 2012 ዓ.ም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሸራተን አዲስ ሆቴል ባዘጋጀው የምስጋና መርሐ ግብር ላይ የሀገረ […]

የ2013 አዲሱን ዓመት አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የእንኳን አደረሳችሁ መግለጫ ተሰጠ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የ2013 አዲሱን ዓመት አስመልክተው በሀገራችን በኢትዮጵያና በመላ ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵውያት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ቅዱስነታቸው የዘመናት ፈጣሪ የሆነው እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ 2012 ዓ/ም ወደ ዘመነ ማቴዎስ 2013 ዓ/ም በሰላም አደረሳችሁ በማለት እግዚአብሔር መነሻም ሆነ፥ መገስገሻ […]

ርእሰ ዐውደ ዓመት የአዲስ ዘመን መጀመሪያ

በኢትዮጵያ ያለፈው ዓመት አልቆ የሚተካው የሚጀመርበት መስከረም አንድ ቀን ስለሆነ በቤተክርስቲያናችን ሥርዓት መሠረት ርእሰ ዐውደ ዓመት ይባላል፡፡ ዘመን ሲያልፍ ዘመን ይተካል፡፡ ትውልድም ሲያልፍ ትውልድ ይተካል፡፡ ለኅልፈትና ለውላጤ የተፈጠረ ፍጡር ሁሉ ወቅትና ጊዜ አለው፡፡ በዚያው በተሰጠው ዘመን ሁሉም ሥራውን ያከናውናል አከናውኖም ያልፋል ያለሥራ የተፈጠረ ፍጡር የለምና፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ፍጥረታትን ፈጥሮ ሲፈጽም “ወርእየ እግዚአብሔር ኵሎ ዘገብረ ከመ […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምእመናን ያሰባሰበችውን 40 ሚሊየን ብር በኦሮሚያ ክልል ጉዳት ለደረሰባቸው ምእመናን አከፋፈለች

ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የምዕራብ አርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ የምሥራቅ ሐረርጌና የሱማሌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የእርዳታ አሰባሳቢ ዐቢይ ኮሚቴ እና የጥናት ኮሚቴ በተገኙበት በዛሬው ዕለት ስለ ተገኘው ድጋፍና አከፋፈሉን በተመለከተ በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡የዐቢይ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ መኮንን ሰሙ በሰጡት መግለጫ በኦሮሚያ ክልል ለተጎዱት ምእመናን ዐቢይ ኮሚቴው ከተቋቋመበት ጊዜ […]

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የደረሰባትን ወቅታዊ ችግር አስመልክቶ መግለጫ ሰጠች

ነሐሴ 20 ቀን 2012 ቅዱስ ፓትርያርኩ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ የጠ/ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብጹዕ አቡነ ያሬድ፣ በርካታ ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተ-ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች: የአ.አ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ፣ እንዲሁም በርካታ የሚዲያ ባለሙያዎችና እንግዶች በተገኙበት በቤተ ክርስቲያኒቱ እና ተከታይ ምእመናኖቿ ላይ እየደረሰ ስላለው ዘግናኝ ፍጅትና መከራ መግለጫ ሰጥታለች። በሀገራችን […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ 8ተኛ ዓመት መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ ለተቸገሩ ህጻናት እርዳታ ተሰጠ

ነሐሴ 10/2012 ዓ.ም በቅዱስነታቸው የመንፈስ ልጆቻቸው የተቋቋመው ፍቅረ ገብርኤል የወንድማማቾች ማኅበር በተባለ በጎ አድራጊ ማኅበር በካቴድራሉ ምግባረ ሠናይ ክፍል አስተባባሪነት በካቴድራሉ አካባቢ ለሚገኙ ተረጂ ህጻናት ለእያንዳንዳቸው 500 ብር፣ 10 ኪሎ ፍርኖ ዱቄት፣ 5 ሌትር ዘይት፣ 5 እሽግ ፓስታ፣ 5 ሳሙና 1 የትምህርት ቤት የተማሪዎች ቦርሳ፣ 1 ደርዘን ደብተር፣ 5 እስክሪብቶ፣ 3 ላጲስ፣ 3 እርሳስ መቅረጫ […]

የአ/አ/ሀ/ስ/ ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃይለገብርኤል ነጋሽ(ቆሞስ) የ2012 ዓ.ም የቅድስት ድንግል ማርያም ጾመ ፍልሰታን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

እንኳን ለ2012 ዓ.ም. ጾመ ፍልሰታ ለማርያም በሰላም አደረሳችሁ!!! “ተንሥእ እግዚኦ ውስተ ዕረፍትከ።አንተ ወታቦተ መቅደስከ።” “አቤቱ ፥ ወደ ዕረፍትህ ተነሥ፥አንተና የመቅደስህ ታቦት።”/መዝ. 132፡8/ ነቢዩ ዳዊት ከአንድ ሺህ ዓመት በፊት ምሥጢር ተገልጦለት፣ ትንቢት ቀድሞለት የጌታችንንና የእመቤታችንን ትንሣኤ ተናግሯል። የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ዕረፍትና ትንሣኤ ደግሞም ዕርገት እንደ ተራ ነገር የሚታይ ሳይሆን የከበረና ምእመናንም በጾም በጸሎት ሁነው የእናታችንን […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ፣ የሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎችና የክፍለ ከተማ ሠራተኞች በጋራ የችግኝ ተከላ መርኃ ግብር አካሄዱ

ሐምሌ 24/2012 ዓ.ም (አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ) ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ❖ ዛሬ ሐምሌ 24/ 2012 ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ቆሞስ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ፣ […]

የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መልአከ ሕይወት አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ በሀገረ ስብከቱ ሥር ከሚገኙ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳዎች ጋር ተወያዩ

ሐምሌ 23 ቀን 2012 የአ.አ ሀ/ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ክቡር አባ ኃ/ገብርኤል ነጋሽ: የሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎች የክፍላተ ከተሞች የሥራ ኃላፊዎችና የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት በሀገረ ስብከቱ የስብሰባ አዳራሽ ጠዋትና ከስአት በተደረገው ውይይት የጾመ ፍልሰታ ሱባኤ አገልግሎት እና የአድባራትና ገዳማት የደመወዝ እስኬል ማስተካከያን በተመለከተ በሁለት አጃንዳዎች ዙሪያ ውይይት ተካሂዷል። የውይይት መርሐ ግብሩን […]

የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በምዕራፈ ሰማዕት ቅዱስ ገብርኤልና ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከበረ

ሐምሌ 19/2012 ዓ.ም (አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ) የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በለምዶ 24 ቀበሌ በሚባለው አካባቢ አዲስ በታነጸው የቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በከፍተኛ ድምቀት ተከበረ፡፡ከወራት በፊት ቤተ ክርስቲያን ለመትከል በተደረገ የምእመናን እንቅሰቃሴ፤ ከፍተኛ ውዝግብ ተነስቶበት የነበረው ይህ ሥፍራ፤ በአካባቢው ምእመናን ከፍተኛ ጥረት እና በሀገረ ስብከቱ የቅርብ ክትትል በአጭር ጊዜ ውስጥ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን