• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

“ምእመናን ልጆቻችን በዚህ ጉባኤ ላይ አመኔታ እንዳያጡ በጣም መጠንቀቅ አለብን” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ

ምእመናን ልጆቻችን በዚህ ጉባኤ ላይ አመኔታ እንዳያጡ በጣም መጠንቀቅ አለብን ሲሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ገለጹ። ቅዱስነታቸው ይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት የመክፈቻ ንግግር ባደረጉበት በዓመታዊው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ላይ ነው። በአሁኑ ጊዜ በሀገራችን፣ በሕዝባችንና በደመ ክርስቶስ በተቀደሱ ክርስቲያን ልጆቻችን ላይ ከበድ […]

የአዲስ አበባ ከተማ ልማት አስተዳደር ጽ/ቤት በቦሌ ደ/ ሳሌም ካቴድራል መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን በጥምቀተ ባሕር ለታቦት ማደሪያ የሚሆን 41ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ያለው የቦታ ካርታ ለአዲስ አበባ ሀ/ሰብከት ጽ/ቤት ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ አስረከበ

የአዲስ አበባ ከተማ ልማት አስተዳደር ተወካዮች በቦሌ ክ/ከተማ ሥር የሚገኘው የቦሌ ደብረ ሳሌም ካቴድራል መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ጥምቀተ ባሕር ለታቦት ማደሪያ የሚሆን 41 ሺህ ካሬ ሜትር ስፋት ያለው የቦታ ካርታ በሀገረ ስብከታቸው ጽ/ቤት ተገኝተው ለቡፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ አስረክበዋል። ብፁዕነታቸው የከተማ ልማት አስተዳደር ተወካዮችን በጽሕፈት ቤታቸው ተቀብለው ያነጋገሩአቸው ሲሆን ቦታውን ከታቦት ማደሪያነቱ በተጨማሪ ለልዩ ልዩ የገቢ […]

በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም በልዩ ልዩ የትምህርት ዘርፍ ሲማሩ የቆዩ ተማሪዎች ተመረቁ

በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም በብሉይ ኪዳን፣ በሐዲስ ኪዳን፣ በሊቃውንት፣ በቅኔ፣ በድጓ፣ በቅዳሴ፣ በአቋቋምና በኆኅተ ስብከት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች በዛሬ ዕለት ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያሪኩ፣ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት በጠቅላይ ቤተ ክህነት በጽረሐ ተዋሕዶ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተመርቀዋል:: ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለተመራቂ ደቀ መዛሙርት […]

የመረጃ ቴክኖሎጂ ትግበራ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት

በመ/ር ዘሩ ብርሃኔ አሁን ባለንበት ዘመን የተቋማትን ውጤታማነት ለማረጋገጥ ቴክኖሎጂ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።ተቋማት ያሏቸውን የዕለት ተዕለት ተግባራት በአግባቡ ማከናወን የሚያስችሏቸውን የመረጃ መሠረተ-ልማቶች እና ሥርዓቶች በመገንባት ተልዕኳቸውን በብቃት ለመወጣት የሚችሉበትን ሁኔታ እየፈጠሩ ይገኛሉ። ከቴክኖሎጂው የሚገኙ ዕድሎችን በአግባቡ ለመጠቀም እንዲቻል ተቋማዊ የቴክኖሎጂ አመራር ሥርዓት መፍጠር እንዲሁም የቴክኖሎጂ አደረጃጀት በአግባቡ መዘርጋት እና ለመዋቅሩ የሚመጥን እውቀት፣ ክህሎት፣ የትምህርት […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ ቤት በአሮጌ ቄራ ባለ 3B + G+15 ሕንጻ ሊገነባ መሆኑን ተገለጸ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በአሮጌ ቄራ ባለ 3B + G+15 ሕንጻ ለመገንባት በዝግጅት ላይ መሆኑን ገልጿል የሕንጻው ግንባታ ዲዛይን ሂደት በኢንጅነር ታምሩ ጥላሁን ለብፁዓን አባቶች ገለጻ ተደርጓል ሕንጻው ለሀገረ ስብከቱ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለውና ከ70 በላይ ፓርክ ያለው መሆኑን ተገልጿል። በገለጻው የተገኙት የጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ያሬድና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና […]

“የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያዋ የትምህርት ሚኒስቴር መሆኗ” ተገለጸ

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያዋ የትምህርት ሚኒስተር ናት” ሲሉ ገለጹ። ብፁዕነታቸው ይህንን የተናገሩት በቀን 13/9/2013 ዓ.ም በአቃቂ መንበረ ሕይወት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በመገኘት ተሠርተው የተጠናቀቁትን G+1 እና G+4 ሕንጻዎችን በጸሎት በመረቁበት ዕለት ነው። G+1 ሕንጻው ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ሲሆን G+4 የሆነው ሕንጻ ደግሞ ዛሬ ከመመረቁ ቀደም […]

“ጻድቅ መሆን የክርስቲያን ሁሉ ግዴታ ነው” ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ

“ጻድቅ መሆን የክርስቲያን ሁሉ ግዴታ ነው” ሲሉ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ገለጹ። ብፁዕነታቸው ይህንን ያሉት በቀን 12/09/2013 ዓ.ም በደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ገዳም ተገኝተው የጻድቁን የአቡነ ተክለሃይማኖትን የፍልሰተ ዐፅሙን ክብረ በዓል ባከበሩበት ነው። ጻድቅ ማለት እውነተኛ ማለት ነው፤ እውነት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ባሕርይ ነው፤ እርሱ እውነት ስለሆነ ርኩሰትንና ውሸትን ይጸየፋል […]

መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፉ መስቀል አደባባይን አሰመልከተው በተናገሩት ቃል ሀገረ ስብከቱ መግለጫ እንደሚሰጥ ገለጸ

ግንቦት 9 ቀን 2013 ዓ.ም በተደረገው የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት የአስተዳደር ጉባኤ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፉ የመስቀል አደባባይ ጉዳይን አስመልክቶ “በቤተክርስቲያን ስም ይቅርታ እንጠይቃለን” ብለው በሰጡት ንግግር ዙሪያ ተወያየ። የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ የሆኑት መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፉ በጉባኤ ፊት ቀርበው ጥያቄም ተጠይቀዋል፡፡ ከተጠየቁት ጥያቄዎች መካከል፦ በቤተክርስቲያኒቱ ስም […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዘመኑን በዋጀ መልኩ በአዲስ መልክ ለማደራጀት የወጣ ውስጠ ደንብ ረቂቅ ቀርቦ ውይይት ተደረገበት

ከሀገረ ስብከት እስከ አጥቢያ ያለው መዋቅራዊና አደረጃጀት የሚያጠና 13 አባላት ያሉት ኮሚቴ ያቀረበው ውሰጠ ደንብ ረቂቅ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በአጥኚው ኮሚቴ የቀረበው ውስጠ ደንቡ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ እየተመራ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ር አካለ ወልድ ተሰማና የየዋና ክፍል ኃላፊዎች በተገኙበት ቀርቦ ውይይት ተርጎበታል። ውስጠ ደንቡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዘመኑን […]

“ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች የኅብረት ቤት ናት” በማለት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ገለጹ

ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች የኅብረት ቤት መሆኗን የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በመልእክታቸው ገለጹ። ቤተክርስቲያን የክርስቲያኖች የኅብረት ቤት ናት፤ በኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ እምነት አንድ የሆኑ ሁሉ የሚጠመቁባት፣ የክርስቶስን ሥጋውንና ደሙን የሚቀበሉባት በመጨረሻም በሰላም የሚያርፉባት ናት በማለት አብራርተዋል። ብፁዕነታቸው ይህንን መልእክት ያስተላለፉት ግንቦት 7 ቀን 2013 ዓ/ም በየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ስር በሚገኘው […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት