• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን አካለወልድ ተሰማ ፣ ዋና ጸሐፊው መ/ር ታዴዎስ ሽፈራው እና ሌሎችም የየክፍሉ ዋና ኃላፊዎች ከአድባራት ና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ጋር ትውውቅ አደረጉ

በዛሬው ዕለት ታህሳስ 15/2013 ዓ/ም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን አካለወልድ ተሰማ ፣የሀገረ ስብከቱ ዋና ጸሐፊ መ/ር ታዴዎስ ሽፈራው የየክፍሉ ዋና ኃላፊዎች፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች በተገኙበት በሀገረ ስብከቱ የስብሰባ አዳራሽ የትውውቅ መርሃ ግብሩ ተካሂዷል።በትውውቅ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ከየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጸ/ቤት ሠራተኞችና በክፍለ ከተማው ሥር ከሚገኙት የአድባራትና የገዳማት አገልጋዮች ጋር ትውውቅ አደረጉ

ዛሬ ታህሳስ 14/2013 ዓ/ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በየካ ደበረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ከየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሠራተኞች እና በክፍለ ከተማው ሥር ከሚገኙት የ46 ገዳማትና አድባራት አብያተ ክርስቲያናት አስተዳዳሪዎች፥ ምክትል ሊቃነ መናብርት፥ ጸሓፊዎች፥ ስብከተ ወንጌል ኃላፊዎች እና የሰንበት ትምህርት ቤት ተወካዮች ጋር የትውውቅ መርሐ ግብር […]

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የዕቅድ ዝግጅት እና አፈጻጸም እንዲሁም ክትትልና ግምገማን በተመለከተ ሥልጠና ተሰጠ

ዛሬ ታህሳስ 13/2013 ዓ/ም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፥ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሓፊና የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፥ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን አካለወልድ ተሰማ ፥ የጉራጌ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ስብሐት ሳህሉ፥ የሁለቱ አህጉረ ሰብከቶች የዋና ክፍል ኃላፊዎች እና […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት አሠራሩን ለማዘመን ከማኑዋል ሲስተም ወደ ኮምፒውተራይዝድ ሲስተም የሚያደርገውን ጉዞ አጠናክሮ ለመቀጠል ለሚመለከታቸው አካላት ስለመረጃ አሰባሰብና አሞላል የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጠ

በዛሬው ዕለት ታህሳስ 13 ቀን 2013 ዓ/ም የጉራጌ እና የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የሀገረ ስብከቱ የየክፍሉ ኃላፊዎች፣የሰባቱ ክፍላተ ከተሞች የሰው ኃይል አስተዳደሮች፣የገዳማትና አድባራት ጸሐፊዎች በተገኙበት በሀገረ ስብከቱ የስብሰባ አዳራሽ ስለ መረጃ አሰባሰብና አሞላል የግንዛቤ ማስጨበጫ ተሰጥቷል። ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ከአሁን በፊት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ረዳት […]

e1

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ጋር በመሆን የጥምቀተ ባሕር ማክበሪያ ስፍራ የሆነውን ጃንሜዳ ጎበኙ

ዛሬ ታህሳስ 11/2013 ዓ/ም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትና እና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን አካለወልድ ተሰማ ጋር በመሆን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታይ ወጣቶች እና በአዲስ አበባ ከተማ ወጣቶች እየጸዳ የሚገኘውን የጥምቀተ ባሕር ማክበሪያ ስፍራ ጃንሜዳን ጎብኝተው […]

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከትሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ያሬድ ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ

ታህሳስ 11 ቀን 2013 ዓ/ም የጉራጌ እና የአዲስ አበባ አህገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ፣ የደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ-ክርስቲያን አስተዳደሪ መልአከ ፀሐይ ተስፋ ማርያም ነጋሽ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኙ የበርካታ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የደብሩ ማኅበረ ካህናት እና […]

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር በሚገኘው በደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የአዲሰ አበባ እና የጉራጌ አህጉር ስብከት ሊቀ ጳጳሰ ብፁእ አቡነ መልከጼዴቅ የተጠናቀቁ የልማት ሥራዎችን ጎበኙ

በጉብኝቱም ወቅት የሀገረ ስብከቱ የሕዝብ ግንኝነት ኃላፊ ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰ፣ የክፍለ ከተማው ቤተ ከህነት ዋና ሥራአሰኪያጅ መልአከ ብርሃን ሩፋኤል የማነ ብርሃን፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ አሚን ለይኩን አበጀ እና የደብሩ የሰበካ ጉባኤ አባላት፡ የደብሩ አገልጋይ ካህናት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ታህሣስ 10 /2013 ዓ/ም የሥራ ጉብኝት አድርገዋል፡፡ የደብሩ አሰተዳደሪ መልአከ አሚን ለይኩን አበጀ “የደብረ […]

የአዲስ አበባና ጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሥራ ጉብኝት አደረጉ ፣ አባታዊ መመሪያም ሰጡ

ታህሳስ 9 ቀን 2013 ዓ/ም የጉራጌ እና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የዋና ክፍል ኃላፊዎች፣ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ትጉሃን ወንዶሰን ገ/ሥላሴ እና የየክፍሉ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በክፍለ ከተማው ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሥራ ጉብኝት አድርገዋል ፣ አባታዊ መመሪያም ሰጥተዋል:: በመርሐ ግብሩ ላይ […]

በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ለመንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት መስጫ የሚውል የግንባታ ቅድመ ጥናት መሪ እቅድ ቀረበ

ታህሳስ 06/ 2013 ዓ/ም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ እና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በደብረ ምጥማቅ ሰአሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ካቴድራል ተገኝተው በቤተ ክርስቲያኑ ይዞታ ላይ የተሰሩ ቤቶችና የተለያዩ ህንጻዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። በጉብኝቱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መምህር አካለወልድ ተሰማ፥ የሀገረ ስብከቱ የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ መ/ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ፥ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት በምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ገብርኤልና ቅ/አርሴማ ቤ/ክ ዓመታዊው የቅድስት አርሴማ ክብረ በዓል በድምቀት ተከብረ

በዛሬው እለት በቀን 6/2013 ዓ.ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ብርሃን ሩፋኤል የማነብርሃን ፣ የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ ሰናይ ባያብል፣የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ፣የደብሩ ካህናትና ዲያቆናት፣የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና በርካታ ምእመናን በተገኙበት በምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ገብርኤልና ቅ/አርሴማ ቤ/ክ ዓመታዊው […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን