• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት የፍቅር ማዕድ መርሐ ግብር ተካሄደ

የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎች መጪውን የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጾመ ፍልሰታ ምክንያት በማድረግ የፍቅር ማዕድ መርሐ ግብር አካሄዱ።የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰ ፍቅር ለሰው ልጆች ከእግዚአብሔር የተሰጠ ልዩ ስጦታ መሆኑን በአጋፔ ማዕድ መርሐ ግብሩ ላይ አብራርተዋል።አብሮ በጋራ የፍቅር ማዕድ መቋደስ መተሳሰብን፣ መረዳዳትን፣ መተዛዘንንና የአብሮነት ስሜትን ያሳድጋልም ብለዋል።ፍቅር […]

በጉራጌ ሀገረ ስብከት በእዣ ወረዳ የሚገኘው የመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል እና አባ ሳሙኤል ገዳም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት ቅዳሴ ቤቱ ተከበረ

በጉራጌ ሀገረ ስብከት እዥ ወረዳ በገጨ ቀበሌ የሚገኘው የመልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል እና አባ ሳሙኤል ገዳም በብፁዓን አባቶች ሐምሌ 25 ቀን 2013 ዓ.ም ተመርቆ በዛሬው ዕለት ቅዳሴ ቤቱ ተከብሯል፡፡በአንድ ኦርቶዶክሳዊ ባለሀብት መሬት ሰጭነት የተመሠረተው አዲሱ ገዳም የመሠረት ድንጋዩ ከተጣለ ከ6 ወራት በኋላ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት መብቃቱ በቀረበው ሪፖርት ተገልጿል፡፡በአካባቢው ምእመናን እና በአንድ ባለሀብት የጋራ ትብብር በከፍተኛ ፍጥነት […]

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የተመራው ልዑክ የጉራጌ ሀገረ ስብከትን የልማት ሥራዎች በመጎብኘት ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

በአዲስ አበባና በጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የተመራና ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተት ልዑክ በጉራጌ ሀገረ ስብከት በአጭር ጊዜ ተሠርተው የተጠናቀቁትን እና በመጠናቀቅ ላይ ያሉትን የልማት ሥራዎችና በቴክኖሎጅ ዘርፍ እየተሠሩ የሚገኙትን የማስፋፊያ ሥራዎችመጎብኘታቸውተገልጿል፡፡ብፁዕነታቸው በሀገረስብከታቸው ከሚያደርጉትሐዋርያዊ አገልግሎት፡ አባታዊ አመራርና ቡራኬ ባሻገር በመንበረ ጵጵስናቸው ግቢ ውስጥ በርካታ የልማት ሥራዎችን ማሰራታቸውን የሀገረ ስብከቱ መረጃ ያመላክታል፡፡ሀገረ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በአሮጌ ቄራ ሊገነባው ያቀደው ባለ 3B+ G+15 ሕንጻ ግንባታ ባርከው አስጀመሩ

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በአሮጌ ቄራ ሊገነባው ያቀደው ባለ 3B + G+ 15 ሕንጻ ግንባታው በጸሎት ባርከው አስጀምረዋል።ብፁዕነታቸው ሕንጻው ለቤተ ክርስቲያን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ያለውና በብዙ ምእመናን በጉጉት የሚጠበቅ መሆኑን በመጥቀስ ግንባታው እንዲፋጠን ትእዛዝ ሰጥተዋል።ሕንጻው ተጠናቅቆ ሥራውን ጀምሮ ማየት የሚናፍቅ ብዙ ነው ያሉት ብፁዕ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በርእሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የተጠናቀቁ ሦስት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አደረጉ፡፡

በአራዳ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር በምትገኘው ርእሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በበጀተ ዓመቱ በደብሩ ሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት፡ በበጎ አድራጊ ኦርቶዶክሳውያንና በማኅበረ ካህናቱ የጋራ ትብብር የተጠናቀቁ ሦስት ፕሮጀክቶች በአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ተመርቀዋል፡፡ከሦስቱ ፕሮጀክቶች መካከል አንዱ የሆነውና በደብሩ ካህናት የአንድ ወር ደመወዝ ስጦታ የታደሰው የዳግማዊ […]

“በሥራ ለተተረጎመ ቦታ በቃል ብዙ ማውራት አስፈላጊ አይደለም “…ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ በርእሰ አድባራት እንጦጦ መንበረ ፀሐይ ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በበጀተ ዓመቱ የተሠሩ የልማት ሥራዎችንና የንጉሡን ቤተ መንግሥትና የቤተ ክርስቲያኑን ውስጣዊ ክፍል ታሪካዊ ይዘቱን በጠበቀ መልኩ የተደረገውን ዕድሳት በመረቁበት ወቅት ያስተላለፉት መልእክት ነው፡፡ብፁዕነታቸው በገዳሙ የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት አስተባባሪነት በደብሩ ካህናትና በበጎ አድራጊ ኦርቶዶክሳውያን የጋራ […]

“ከሰው የሚጠበቀው ማመንና መታዘዝ ነው” ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ

የሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በቦሌ ክፍለ ከተማ በተለምዶ 24 በሚባለው አካባቢ በሚገኘው በምዕራፈ ሰማዕታት ቅዱስ ገብርኤልና አርሴማ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከብሮ ውሏል፡፡የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ክብረ በዓሉን የተመለከተ ትምህርት አስተላልፈዋል።የሕጻን ቅዱስ ቂርቆስንና የእናቱን የቅድስት እየሉጣን የእምነት ጽናት አብራርተዋል።በሕይወታቸውና በልባቸው ውስጥ ሰማያዊውን ንጉሥ ስላነገሡ ምድራዊው ንጉሥ በወታደሮቹ […]

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ መመሪያ ሰጭነት ተገንብቶ የተጠናቀቀው የአዳሪ ትምህርት ቤት ደቀ መዛሙርትን ተቀበለ

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ መመሪያ ሰጭነት በጉራጌ አህጉረ ስብከት ተገንብቶ የተጠናቀቀው የአዳሪ ትምህርት ቤት ደቀ መዛሙርትን ተቀበለ።ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ለደቀመዛሙርቱ “የእንኳን ደህና መጣችሁ” መልእክት አስተላልፈውላቸዋል።ብፁዕነታቸው የትምህርት ቤቱ መገንባት ዋናው ዓላማ ካህናትን በማሰልጠን ምእመናንን በመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽ ለማድረግ እንደሆነ አውስተዋል።አያይዘውም ካህናቱ በትምህርት ቆይታቸው የሚሰጣቸውን ሥልጠናዎች በአግባቡ በመውሰድ መንፈሳዊ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ […]

የብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ አራተኛ በዓለ ሲመት በድምቀት ተከብሮ ዋለ

የብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ አራተኛ በዓለ ሲመት በወልቂጤ ከተማ በደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ካቴድራል በድምቀት ተከብሮ ዋለ።ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ባስተላለፉት መልእክት በዓሉ የአንድ መንፈሳዊ አባት በዓል ሳይሆን የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በዓል ነው ሲሉ ገልጸዋል።የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለበርካታ ዘመናት ከግብጽ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን በሚመጡ ጳጳሳት ስትተዳደር እንደነበር አውስተዋል።ይህም ለቤተክርስቲያን በተለይ […]

“አስከፊ የኑሮ ሁኔታና ቅንነት ከጎደለው የካራን አስተሳሰብ ወጥተን የዕረፍት ምድራችን ወደ ሆነችው ከነዓን እንግባ“…ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ

የአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በርካታ አገልጋዮችና ኦርቶዶክሳዊ ምዕመናን በተገኙበት ተከብሮ ውሏል፡፡በአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ጋባዥነት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ ኮሌጅ ፕሬዘዳንትና የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ፊልጶስ የዕለቱን ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል፡፡በትምህርታቸውም የእምነት አርበኛ የሆነውን የአብርሃምን የጥሪ ሕይወት: ለጠራው […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት