• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በቆጠር ገድራ መካነ ቅዱሳን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት አንድነት ገዳም ተከብሮ ዋለ!

የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በጉራጌ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው ቆጠር ገድራ መካነ ቅዱሳን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት እና አቡነ ሀብተማርያም አንድነት ገዳም አዳሪ መንፈሳዊ ት/ቤት ተከብሮ ውሏል። ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ክብረ በዓሉን የተመለከተ ትምህርት ሰጥተዋል። ጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ከራሳቸው ፍላጎት ይልቅ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በመፈጸምና በመከተል መልካም ፍሬ […]

“ኢትዮጵያ የእግዚአብሄር ንዋየ ቅድሣት ሀገር ናት !!!” ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ዛሬ ህዳር 21 ቀን 2014 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በተገኙበት በደብረ ምጥማቅ ሠአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ካቴድራል የእመቤታችን ንግሥ ተከብሮ ውሏል። በአውደ ምህረቱ የካቴድራሉ መምህራን “ሙሴኒ ርዕያ ሀገር ቅድስት የሚለውን እና አባ አቡነ አባ መምህርነ አባ መልከጴዴቅ” የሚለውን ለብፁዕነታቸው በሽብሻቦ አቀርበዋል። የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችም ታቦተ ሕጉ […]

ደቡብ ክልል የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ኮሌጅ ተመረቀ!

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ መመሪያ ሰጭነት በጉራጌ አህጉረ ስብከት ተገንብቶ የተጠናቀቀው መንፈሳዊ ኮሌጅ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በጸሎት ተባርኳል።ኮሌጁም “ዜና ማርቆስ ዘምሁር መንፈሳዊ ኮሌጅ” ተብሎ ተሰይሟል። መንፈሳዊ ኮሌጆች ትውልዱን በመንፈሳዊ ሕይወት ለማነጽ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ጠቅሰዋል።አያይዘውም ደቀመዛሙርትን በማሰልጠን ምእመናንን በመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽ ለማድረግ ብዙ መንፈሳዊ ኮሌጆች ለቤተክርስቲያኒቱ እንደሚያስፈልጉም […]

የ 2014 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበርን በተመለከተ በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ውይይት ተካሄደ

ነሐሴ 25 ቀን 2013 ዓ.ም( አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ )መጪውን የ 2014 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበርን በተመለከተ በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ውይይት ተካሄደ።በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የዘንድሮውን የመስቀል ደመራ በዓል የሚያዘጋጀው የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን በጥሩ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ በቀለ ተሰማ ለብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት […]

የጻድቁ አቡነ ተክለሃይማኖት የዕረፍት በዓል በመርካቶ ደብረ አሚን ተክለሃይማኖት ገዳም ተከብሮ ዋለ

ነሐሴ 24 ቀን 2013 ዓ.ም( አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ )ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዕለቱን በተመለከተ ትምህርት አስተላልፈዋል።ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ይህንን ዓለም በመናቅና ሕይወታቸዉን ለእግዚአብሔር በመስጠት እንደኖሩ ገልጸዋል።ጻድቁ በጾም፣ በጸሎትና በምስጋና ሕይወት እንደኖሩም ጠቅሰዋል።አያይዘውም ወንጌልንም በመላው ኢትዮጵያ እየተዘዋወሩ ለምእመናን መስበካቸውን አውስተዋል።በመድኀኒታችንና በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም የተለያዩ ተአምራትን ስለማድረጋቸውም […]

የቦሌ ክፍለ ከተማን ሥራ እዚሁ መጥቼ እሠራለሁ……ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ

(ነሐሴ 22 ቀን 2013 ዓ.ም )(አዲስ አበባ÷ኢትዮጵያ)የአዲስ አበባ እና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ሁለንተናዊ ዕድሳት ተደርጎለት ለምርቃት የበቃውን የቦሌ ክፍለ ከተማ ጽ/ቤት ነሐሴ 22 ቀን 2013 ዓ.ም በመረቁ ወቅት ያስተላለፉት መልእክት ነው፡፡ምቹ የሥራ አካባቢን ለመፍጠር ታሳቢ አድርጎ የተጀመረው ሁለንተናዊ ዕድሳት በአጭር ጊዜ በመጠናቀቁ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፡ የጠቅላይ ቤተ ክህነትና […]

ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሠራተኞች መሰረታዊ የቴክኖሎጂ ሥልጠና መስጠት ተጀመረ

(ነሐሴ 22 ቀን 2013 ዓ/ም) አዲስ አበባ: ኢትዮጵያየአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የዋና ክፍል፣ የክፍልና ልዬ ልዩ ሠራተኞች በሀገረ ስብከቱ የኮምፒዩተር ማሰልጠኛ ማዕከል መሰረታዊ የቴክኖሎጂ ሥልጠና መውሰድ ጀምረዋል።ሥልጠናው በብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መልካም ፈቃድ በሀገረ ስብከቱ አይቲና ዶክሜንቴሽን ዋና ክፍል አስተባባሪነት የተዘጋጀ ነው።ሥልጠናው የሚሰጠው ሥልጠና ለመውሰድ የተዘጋጀውን ቅጽ ለሞሉ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጾመ ፍልሰታ መግቢያ አስመልክተው መመሪያዎችን አስተላለፉ

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የእመቤታችንን የቅድስት ድንግል ማርያምን ጾመ ፍልሰታ መግቢያ አስመልክተው መመሪያዎችን አስተላለፉ።ብፁዕነታቸው መመሪያዎችን ያስተላለፉት ለአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎችና ቄሰ ገበዞች ነው።“ለሁሉም ጊዜ አለው” የሚለውን የእግዚአብሔርን ቃል መነሻ በማድረግ ከ ነሐሴ 1 ቀን እስከ ነሐሴ 16 ቀን ወይም አስከ 21 ቀን የምንጾምበት ጊዜ ነው ብለዋል።አያይዘውም ወደ ፈጣሪያችን አብዝተን የምንጸልይበት […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ያለፈውን የበጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትንና የመጪውን የበጀት ዓመት ዕቅድ እየገመገመ ይገኛል

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ያለፈውን የ2013 ዓ.ም የበጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትንና የመጪውን የ2014 ዓ.ም የበጀት ዓመት ዕቅድን አስመልክቶ በመገምገም ላይ ይገኛል።በአዲስ አበባና በጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ መመሪያ ሰጭነት ከሐምሌ 15 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ የግምገማ መርሐ ግብሩ በመካሄድ ላይ ነው።የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ራሱን ችሎ በሊቀ ጳጳስ እንዲመራ […]

ሁለት ዓመት ከስድስት ወር የፈጀው አለመግባባት በሰላም ተፈታ

በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችና ሰበካ ጉባኤው መካከል ተከስቶ የነበረው አለመግባባት በሰላም ተፈታ።መርሐ ግብሩ በብፁዕ አቡነ ማርቆስ የጠቅላይ ቤተክህነት የስብከተ ወንጌል መምሪያ የበላይ ጠባቂ ጸሎትና ቡራኬ ተከፍቷል።የችግሩ ምክንያት በሰንበት ትምህርት ቤቱና በሰበካ ጉባኤው መካከል ሁለገብ ሕንጻን በመገንባት በኩል የሃሳብ ልዩነት በመፈጠሩ እንደሆነ ተብራርቷል።በአዲስ አበባና በጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት