• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት በደብረ ገሊላ ቅዱስ አማኑኤል ካቴድራል ቤ/ክ ዓመታዊው የቅዱስ አማኑኤል ክብረ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል

በዛሬው ዕለት ታኅሣሥ 28 ቀን 2013 ዓ.ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፈ፣ የአዲስ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ሃይማኖት ጸጋዬ ገ/ዮሐንስ፣ የካቴድራሉ አስተዳዳሪ መ/ገነት ቀሲስ በቀለ ዘውዴ፣ የካቴድራሉ ጸሐፊ መ/ሥርዓት እጓለ፣ የካቴድራሉ ካህናትና ዲያቆናት፣የካቴድራሉ […]

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ

ብፁዕነታቸው “በእንኳን አደረሳችሁ መልእክታቸው” እንደገለጹት የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት ስናከብር ” ሕጻን ተወልደ ለነ ወልድ ተውህበ ለነ” (ት.ኢሳ 9፥6) ሕጻን ተወልዶልናልና፤ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና የሚለውን መለኮታዊ ቃል በውስጣችን በማሰብ ማክበር እንደሚገባን መልእክት አስተላልፈዋል።ክብረ በዓላትን ስናከብር በአንዳንዶች ዘንድ እንደሚታው ሥጋዊ ነገሮች ላይ ብቻ ትኩረት ከማድረግ ተቆጥበን፤ይልቁንም ከምንም በላይ መንፈሳዊ መልእክቱና ይዘቱ ላይ ትኩረት ልናደርግ […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገና በዓልን አስመልክቶ ለስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ድጋፍ አደረገ

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በሀገረ ስብከቱ ምግባረ ሰናይ አስተባባሪነት የተሰበሰበ የምግብ፣የልብስ፣ የጤናና የትምህርት ቁሳቁሶችን ለስለእናት የበጎ አድራጎት ድርጅት አስረክቧል፡፡ድጋፉ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳሰ ለስለ አናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ፕሮግራም ኃላፊ ሙሉ ጌታ በቀለ አስረክበዋል፡፡ ብፁዕነታቸው አንድ ቀን ድርጅቱን እንደሚጎበኙ ገልጸዋል፡፡ስለአናት የበጎ አድራጎት ድርጅት ከፍተኛ የአእምሮ የአካል ጉዳት ያለባቸውና […]

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳሰ ብፁዕ አቡነ መልከፄዴቅ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው በቃሉ ተራራ አቡነ ኃብተማርያም ገዳም የሥራ ጉብኝት አደረጉ

ታኅሣሥ 26 ቀን 2013 ዓ/ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳሰ ብፁዕ አቡነ መልከፄዴቅ በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የሚገኘው በቃሉ ተራራ አቡነ ኃብተማርያም ገዳም የሥራ ጉብኝት አድርገዋል። ብፁዕነታቸው በገዳሙ በሌሊት ተገኝተው የነግህ ጸሎተ ኪዳን አድርሰዋል።በቦታው መልአከ ሕይወት ቆሞሰ አባ ወልደ ኢየሱስ የሀገረ ስብከቱ የካህናት አሰተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ፣ የገዳሙ አሰተዳዳሪ ክቡር […]

በዓለ ጥምቀት የሀገር እና የዓለም ሕያው ቅርስ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው መንፈሳዊ የምሥጋና መርሐ ግብር በጃንሆይሜዳ (ጃንሜዳ) ተደረገ

ታህሳስ 25 ቀን 2013 ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊና የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ፡ የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፡ የሶማሌና ምሥራቅ ሀረርጌ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳዳደር ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፡ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ር አካለወልድ ተሰማ፡ የጠቅላይ ቤተ […]

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በልደታ ክፍለ ከተማ ሥር የሚገኘው የገዳመ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ጎበኙ

ታኅሣሥ 25 ቀን 2013 ዓ.ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በልደታ ክፍለ ከተማ ሥር የሚገኘው የገዳመ ኢየሱስ ቤተ ክርስቲያን ጎብኝተው ምእመናኑን ባርከዋል። በቦታው መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ነጋሽ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ፣ ሊቀ ትጉኃን ደማሙ የልደታ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት የሰው ኃይል ክፍል ኃላፊ፣ […]

አዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት በዳግማዊ ደብረ ሊባኖስ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ዓመታዊው የጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የልደታቸው ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ

በዛሬው ዕለት ታኅሣሥ 24 ቀን 2013 ዓ.ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ነጋሽ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ፣ የገዳሙ አስተዳዳሪ መልአከ አሚን አባ ኃይለማርያም፣የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣የገዳሙ አገልጋዮችና የሰንበት ትምህርት […]

የአዲስ የአበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት በደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል የብሥራት ክብረ በዓል በድምቀት ተከበረ

ታህሳስ 22 ቀን 2013 ዓ/ም የጉራጌ እና የአዲስ አበባ አህገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ: የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ነጋሽ፡ የነፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መ/ም ዘካርያስ ዐዲስ ፡የደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተ-ክርስቲያን አስተዳደሪ መልአከ አሚን ለይኩን አበጀ፡ የደብሩ ዋና ጸሐፊ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት በመንበረ መንግሥት /ግቢ/ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዓመታዊው የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል

በዛሬው ዕለት ታህሳስ 19 ቀን 2013 ዓ.ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ ብፁዕ አቡነ ሰላማ የታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያምና የመንበረ መንግሥት /ግቢ/ ቅዱስ ገብርኤል ገዳማት የበላይ ጠባቂ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ መ/ብ ሳሙኤል ደምሴ፣የአራዳና ጉለሌ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/አሚን ቆሞስ አባ ላ/ማርያም […]

የቀበና ምዕራፈ ጻድቃን አቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል አዲሱ መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ተመረቀ

ታኅሣሥ 18/2013 ዓ/ም በካሳንችስ ዓድዋ ድልድይ የሚገኘው አዲሱ የተሠራ የአቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅ/ገብርኤል መቃኞ ቤተ ክርስቲያን ተመርቆ ተባርኳል። በመርሃ ግብሩ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ ዋና ክፍል ኃላፊ መ/ብ ሳሙኤል ደምሴ፥ የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ እሰኪያጅ መጋቤ ትፍስሕት ግርማ አሰፋ፥ የየካ ክፍለ ከተማ ጽ/ቤት ሠራተኞች፥ የደብሩ ዋና አስተዳዳሪ መ/ሰላም አበበ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን