• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

“እሱ እንደ ተዋሐደን እኛም እርስ በርሳችን ተዋሕደንና አንድ ሆነን በፍቅርና በሰላም እንድንኖር ነው” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደትን አስመልክቶው በመላ ዓለም ለሚኖሩ አማንያን የእንኳን አደረሳችሁ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል። ቅዱስነታቸው በመልእክታቸው “እሱ እንደ ተዋሐደን እኛም እርስ በርሳችን ተዋሕደንና አንድ ሆነን በፍቅርና በሰላም እንድንኖር ነው” ብለዋል። […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ!

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደትን አስመልክተው የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ። መልአኩ የተናገረውን ” …ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ፤ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና” (ሉቃ 2፥10-11) የሚለውን መለኮታዊ ቃል በውስጣችን በማሰብ ማክበር እንደሚገባን አሳስበዋል። ክብረ በዓላትን ስናከብር በአንዳንዶች […]

ለመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እድሣት የድጋፍ ጥሪ ቀረበ

መላው ኢትዮጵያውያን ዕድሜ ጠገብ የአገር ቅርስ ለሆነው መንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ዕድሳት የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ካቴድራሉ ጥሪ ማቅረቡ ተሰምቷል፡፡ የካቴድራሉ ዋና አስተዳዳሪ ሊቀ ሥልጣናት ቆሞስ አባ ሲራክ አድማሱ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፤ ካቴድራሉ ከተገነባ ለረጅም ዓመታት ሳይታደስ በመቆየቱ በጣሪያው ላይ የመሰንጠቅ አደጋ ደርሶበት ውሃ እያፈሰሰ ይገኛል። ካቴድራሉ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ከሚሰጠው መንፈሳዊ አገልግሎት ባሻገር በቅርስነቱ በርካታ […]

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ያካሄደውን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ በተመለከተ ተጨማሪ መረጃዎች!

የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊ/ት ወንድወሰን ገ/ሥላሴ “የ2013 ዓ.ም የበጀት ዓመት የሥራ ሪፖርትን” ለጉባኤው አቅርበዋል። ሪፖርቱ በሰበካ ጉባኤ፣ በስብከተ ወንጌል አገልግሎት፣ በሰው ኃይል አስተዳደር፣ በሂሳብና በጀት፣ በቁጥጥር፣በሰንበት ት/ቤት፣ በትምህርትና ሥልጠና፣ በዕቅድና ልማት፣ በቅርሳ ቅርስ እና በምግባረ ሠናይ ክፍሎች የተከናወኑ ሥራዎችን ያካካተ ነበር። በበጀት ዓመቱ ክፍለ ከተማው አብዛኞቹን ዕቅዶች በሥራ ላይ እንዳዋለ ከሪፖርቱ ተደምጧል። የብፁዕ […]

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት በሥሩ ካሉት አድባራትና ገዳማት ጋር በመሆን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤን እያካሄደ ይገኛል!

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሥር ከሚገኙት ከሰባቱ ክፍላተ ከተማ አንዱ የሆነው የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ከአድባራቱና ገዳማቱ ጋር በመሆን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤን እያካሄደ ይገኛል። ጉባኤው እየተካሄደ ያለው በቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ነው። ሊ/ት ወንድወሰን ገ/ሥላሴ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ በጉባኤው ላይ ለተገኙት “የእንኳን ደህና መጣችሁ” መልእክት […]

“ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለኢትዮጵያ የተሰጡ ቅዱስ አባታችን ናቸው”… ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ

የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የልደት ክብረ በዓል በመርካቶ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱን ጨምሮ በርካታ ካህናትና ምእመናን በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ በመርካቶ ደብረ አሚን […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ለ53 አህጉረ ስብከት የ106 ሚልዮን ብር ድጋፍ አደረገ

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የሚመራው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ለ53 አህጉረ ስብከት የ106 ሚልዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል። በሀገረ ስብከቱ ድጋፍ የተደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥቅምት 16 ቀን 2014 ዓ/ም በወሰነው ውሳኔ መሠረት መሆኑን ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምቱ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባው ላይ በቅቱን ተከትሎ በተለያየ ምክንያት ችግር ለደረሰባቸውና የምጣኔ […]

የቤተ ክርስቲያን ታላላቅ አባቶችን በማፍራት የሚታወቀው የፈለገ ቅዱሳን ሰ/ት/ቤት 43ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አከበረ!

የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅን ጨምሮ ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን ያፈራው የወልቂጤ ደ/ፅ/ቅ/ማርያም ፈለገ ቅዱሳን ሰ/ት/ቤት 43ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ከታኅሣሥ 15 እስከ 17 ባሉት ቀናት ውስጥ በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በመርሐ ግብሩ ላይ የሦስት ቀን የዐውደ ምኅረት ጉባኤ እና በከተማው ለሚገኙ የሰ/ ት/ቤቶች የአገልግሎት ሥልጠና ተሰጥቷል። በተያያዘም የምክክር […]

የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በድምቀት ተከብሮ ዋለ

የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በርካታ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውላል። በበዓሉ በሊቃውንት ‘ወረደ መልአክ ሊቀ መላእክት ኃበ ሠለስቱ ደቂቅ’ የሚል ያሬዳዊ ዝማሬ ሲቀርብ፣በገዳሙ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ‘ገብርኤል ምልአኒ መንፈሰ ልሳን፣ ለተናብቦ መንፈሰ […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት