• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይሜኖት ወልዱ የዘውዲቱ መሸሻ የህጻናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎትና ልማት ማሕበር ጎበኙ።

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይሜኖት ወልዱ በሽሮ ሜዳ ቁስቋም ቤተ ክርስቲያን አካባቢ የሚገኘው የዘውዲቱ መሸሻ የህጻናትና ቤተሰብ የበጎ አድራጎትና ልማት ማሕበር ጎብኝተዋል። ክቡር ዋና ሥራ አስኪያጁ ተቋሙን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን “ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱን ግን ቢጎድል ምን ይጠቅመዋል?” ማቴ 16፥26 የሚል የእግዚአብሔር ቃል መነሻ አድርገው አስተምረዋል። የሰው ልጅ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ!

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ጥምቀት አስመልክተው ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ። በዓሉን ስናከብር “የበዓሉን መንፈሳዊ ጭብጥ መልእክት” ከልብ በመረዳትና በመገንዘብ መሆን እንዳለበት ብፁዕነታቸው አሳስበዋል። ሐዋርያው የተናገረውን ” …ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን፤ ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን […]

በዓለ አስተርእዮ

አስተርእዮ፡- ቃሉ ግእዝ ነው፡፡ አስተርእዮ ማለትም መገለጥ፣ መታየት ማለት ነው፡፡ በግሪክ ቋንቋ ኤጲፋንያ ይባላል ኤጲፋንያ ማለት መገለጥ፤ መታየት ማለት ነው፡፡ አሁን ያለንበት ዘመን ዘመነ አስተርእዮ ይባላል የመገለጥ፣ የመታየት ዘመን ማለት ነው፡፡ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ሰው ሆኖ የተገለጠበት ዘመን ስለሆነ እና እንዲሁም በጥምቀቱ አንድነቱን ሦስትነቱን […]

የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ተጠናቆ ለበዓል አከባበር ሥርዓቱ ዝግጁ ሆነ

ከአንድ ወር በፊት የ2014 ዓ.ም የጥምቀት በዓልን በማስመልከት በዘመናት አገልግሎት ምክንያት በእጅጉ ተጎሳቁሎ የነበረውን የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀትን ለማደስ በተደረገው እንቅስቃሴ በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔና በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አሳሳቢነት የግንባታ ሥራው የተጀመረው የጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ መጠናቀቁና ለጥምቀት በዓል ዝግጁ መሆኑ ታውቋል። በምዕራፍ አንድ የግንባታ ሥራ ከተከናወኑት ተግባራት መካከል የባህረ ጥምቀቱን ገንዳ በአዲስና […]

የቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓል በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በድምቀት ተከብሮ ዋለ።

የቅድስት ሥላሴ ክብረ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፥ ሊቃውንተ ቤተ ክስርስቲያንና በርካታ ምእመናን በተገኙበት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል  በድምቀት ተከብሮ ውሏል። በዓውደ ምሕረት መርሐ ግብሩ “ዮም መላእክት ይዬብቡ ወሊቃነ መላእክት ይዜምሩ፤ እስመ መድኅን መጽአ ውስተ ዓለም ለቢሶ ሥጋነ”የሚል ያሬዳዊ ወረብ በሊቃውንት ሲቀርብ፤ በካቴድራሉ ሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ወይቤላ አብ ለማርያም አምጣንየ አምጣነኪ አዝማንየ አዝማነኪ […]

የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት በጦርነት ለተጎዱ ወገኖች የሚውል 15,000,000 ብር የሚገመት የአልባሳት፣ የአስቤዛ እና የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ!

የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት አብያተክርስቲያናትን በማስተባበር 15,000,000 ብር የሚገመት የአልባሳት፣ የአስቤዛ እና የተለያዩ የቁሳቁስ ድጋፍን በማሰባሰብ በጦርነት ለተጎዱ ወገኖች ዕርዳታ አደረገ። የቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ብ ሩፋኤል የማነብርሃን የዕርዳታውን ዓላማ እና አሰባሰብ በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የዕርዳታው ዋና ዓላማ በሀገራችን በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ከሞቀ ቤታቸውና ከቀያቸው ለተፈናቀሉ እና ለተጎዱ ወገኖች የሚውል […]

የኢትዮጵያና የኬንያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤያት የጋራ ስምምነት ተፈራረሙ !!!

በምሥራቅ አፍሪካ የቀጠናውን የሰላምና የመከባበር ዕሴት ለመገንባት እንዲሁም ጽንፈኝነትን ለመከላከል የሚያስችል የጋራ ስምምነት ሰነድ ተፈራረሙ። ስምምነቱን የተፈራረሙት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና የኬንያ የሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ ናቸው። ስምምነቱን የኢትዮጵያ ሐይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ አባላትና የኬንያ የተቋሙ ዳይሬክተርና ዋና ጸሐፊ ተፈራርመዋል። በስምምነቱ ወቅት ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ጉባኤው በምሥራቅ አፍሪካ ሀገራት ከሚገኙ የሃይማኖት ተቋማትና […]

“በቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ አንደራደርም” …ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ

ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷም ነፍስ ነስቶ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደበትን ዕለት በማስመልከት ዛሬ  በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የስብሰባ አዳራሽ በተዘጋጀ የእንኳን አደረሰዎ መርሐ ግብር ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ስለ መስቀል አደባባይ ጉዳይ ያስተላለፉት አጭር መልክት ነው። የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በዚሁ ጉዳይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር […]

የመስቀል አደባባይ ባለቤት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መሆኗ ለጥያቄ የሚቀርብ አይደለም ….ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ

ዛሬ ጥር 1 ቀን 2014 ዓ.ም 9:00 ሐዋርያ ዘለዓለም የተባለ የወንጌላውያን አማኞች ኅብረት አባል የሆነ ፓስተር መስቀል አደባባይ ላይ ለጠራው የአምልኮ ፕሮግራም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በጽህፈት ቤታቸው ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥተዋል። ብፁዕነታቸው የፓስተሩ የመስቀል አደባባይ ፕሮግራም እንዲሰረዝ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከክብርት ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ጋር በስልክ መነጋገራቸውን ገልፀው ማሰረዝ ግን አልተቻለም ብለዋል። እንዲህ […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ደቀመዛሙርትን፣ መነኮሳትንና የዩንቨርስቲ ተማሪዎችን በመጎብኘት የልደት በዓልን አከበሩ!

የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን በዓለ ልደት ደቀመዛሙርትን፣ መነኮሳትንና የዩንቨርስቲ ተማሪዎችን በመጎብኘት አከበሩ። ብፁዕነታቸው በወልቂጤ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ግቢ በመገኘት በዚያው ከሚኖሩት አበው መነኮሳት፣ የአብነት መምህራንና ደቀ መዛሙርት ጋር በመሆን በዓለ ልደትን አክብረዋል። ደቀ መዛሙርቱ የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደትን በተመለከተ ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል። […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን

    © በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት