• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የትንሣኤን በዓል አስመልክተው ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ያስተላለፉት መልእክት

“ተንሥአ በከመ ይቤ” (ማቴ ፳፰፥፮)እንደ ተናገረ ተነሥቶአል (ማቴ 28፥6) ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱና ዋነኛው የትንሣኤ በዓል ነው። ትንሣኤ “ተንሥአ” ከሚለው የግዕዝ ግስ የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙም መነሣትን ያመለክታል፤ ከሞት በኋላ በነፍስ ብቻ ሳይሆን በሥጋም ጭምር ሕያው ሆኖ መነሣትን የሚገልጽ ቃል ነው። “ኃጢአተኞችን ሊያድን ክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጣ የሚለው ቃል የታመነና ሁሉ […]

የኢየሱስ ክርስቶስን የስቅለት በዓል አስመልክተው ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ያስተላለፉት መልእክት

ፍጹም ፍቅር ጊዜው ከዛሬ 2000 ዓ.ም ገዳማ በፊት ነበር ዕለቱ ደግሞ ዕለተ አርብ ። ለዘመናት በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ዕንቅፋት ሆኖ የቆየው የኃጢአት ግድግዳ የፈራረሰበትና በአንጻሩ ደግሞ ጽኑ የምሕረትና የጽድቅ ድልድይ የተገነባበት፣ በሥልጣን ላይ የነበረው ሞት በጊዜ ገደብ ምክንያት ሥልጣኑን ለሕይወት ያስረከበበት፣ ዓመተ ፍዳም ከአቅም ማነስ የተነሣ መንበረ መንግሰሥቱን ለመሪው ለዓመተ ምህረት የለቀቀበት ክስተቶች የተከናወኑበት ዕለት […]

“በሞቱ ከመሰልነውም: በትንሳኤው እንመስለዋለን” ሮሜ. 6:5

ለአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ፅ/ ቤት ሰራተኞች፣ ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች እንዲሁም ለሁሉም ምእመናን በያላችሁበት መልካም ሰሙነ ህማማት( የፀሎት፣ ስግደት እና የቅዱሳት መፃህፍት የንባብ ጊዜ) ይህንላችሁ:: ትንሳኤውን ለማየት በህማማቱ በኩል ማለፍ/ መሳተፍ እንደሚገባ ሲያመለክት ቅዱስ ጳውሎስ “ሞቱን በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከሞት፣ ትንሳኤውን በሚመስል ትንሳኤ ከእርሱ ጋር እንነሳለን” ያለውን ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ታደርገዋለች: […]

የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ የሕማማትና የትንሣኤ በዓላትን አስመልክቶ መመሪያ አስተላለፉ!!

ሚያዚያ 14 ቀን 2013 ዓ.ም የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ር አካለወልድ ተሰማና ልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በሀገረ ስብከቱ የስብሰባ አዳራሽ የሰሙነ ሕማማትና የትንሣኤ በዓላት አከባበር መንፈሳዊ ይዘቱን ጠብቆ እንዲከበር አባታዊ መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡ከሆሳእና ጀምሮ ያሉት የሕማማትና የትንሣኤ በዓላት ልዩ ልዩና በርካታ መንፈሳዊ ሥርዓቶች የሚፈጸሙባቸው በዓላት በመሆናቸው […]

በዓለ ሆሣዕና

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኙ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱ የሆሣዕና በዓል ነው፡፡ ስለዚህ በዓል አስቀድሞ ትንቢት ተነግሯል፤ ከትንቢቶቹም አንዱ እንደሚከተለው ተጠቅሷል፡፡ “አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በይ እነሆ ንጉሥሽ ትሑት ሆኖ በአህያና በአህያይቱ ውርንጫ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል” /ትን. ዘካ. 9፡9/ከዚህም ጋር ስለበዓለ ሆሣዕና አራቱም ወንጌላውያን […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በተገኙበት በምሁር ኢየሱስ ገዳም የእኩለጾም (የደብረ ዘይት) ክብረ በዓል በድምቀት ተከብሮ ዋለ

በቀን 26/2013 ዓ.ም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካህናት አስተዳደር ዋና ክፍል ኃላፊ መልአከ ሕይወት አባ ወልደ ኢየሱስ ሰይፈ፣ የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ዳዊት ታደሰ፣ የጉራጌ ሀገረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የገዳሙ አስተዳዳሪ መ/ር አባ ዘኢየሱስና በርካታ ምእመናን በተገኙበት ዓመታዊው የእኩለጾም […]

ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በቦሌ ቡልቡላ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ሚካኤልና ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም በመገኘት ገዳሙ በተጠናከረ መልኩ እንዲገደም መመሪያን አስተላለፉ

በዛሬው ዕለት መጋቢት 24 ቀን 2013 ዓ/ም የጉራጌ እና የአዲስ አበባ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መ/ር አካለወልድ ተሰማ፣ከሀገረ ስብከቱ የዋና ክፍል ኃላፊዎች፣ ከክፍላተ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጆችና ከአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ጋር በመሆን በቦሌ ቡልቡላ ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ሚካኤልና ተክለሃይማኖት አንድነት ገዳም በመገኘት ገዳሙ ከዚህ በፊት […]

በመ/ፓ/ጠ/ጽ/ቤት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ በኩል ሲካሄድ በቆየው በ39ኛው አገር አቀፍ ስምሪት ላይ በችግሮችና በመፍትሔዎች ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

በቀን 23/2013 ዓ.ም በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ጽርሐ ተዋሕዶ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ በተካሄደው መርሐ ግብር ላይ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ያሬድ፣ የመ/ፓ/ጠ/ጽ/ቤት የሰበካ ጉባኤ ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኮንን፣ የመ/ፓ/ጠቅላይ […]

ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ በተገኙበት በቦሌ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት አዘጋጅነት ለሁለት ቀናት እየተሰጠ የቆየው ስልጠና በዛሬው ዕለት ተጠናቀቀ!!

መጋቢት 22 ቀን 2013 ዓ/ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ሥር ለሚገኙ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊዎች በክፍለ ከተማው የትምህርትና ስልጠና ክፍል አስተባባነት በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የስብሰባ አዳራሽ ለሁለት ቀናት እየተሰጠ የቆየው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በብጹዕ አቡነ መልከጼዴቅ መመሪያ ሰጭነት በዛሬው ተጠናቋል፡፡በዕለቱ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ም/ሥራ አስኪያጅ መጋቤ ጥበብ ምናሴ ወልደ ሐና […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን