• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

በምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ገብርኤል፣ ቅ/አርሴማ ወአቡነ አዳም ቤተ ክርስቲያን የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ ዓመታዊ ክብረ በዓል በድምቀት ተከብሮ ዋለ።

በምሥራቀ ፀሐይ ቅ/ገብርኤል፣ ቅ/አርሴማ ወአቡነ አዳም ቤተ ክርስቲያን የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ ቅዳሴ ቤቷ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና እጅግ በርካታ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውሏል። በበዓሉ በሊቃውንት “ሃሌ ሉያ ቤተ ክርስቲያን፡ መስቀለ ክርስቶስ መሠረታ…፣ በደብሩ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራንም “እንተ ተሐንጸት በእደ ካህናት፡ ወተቀደሰት ቤተ ክርስቲያን በአፈ ጳጳሳት” የሚል ያሬዳዊ ዝማሬ ተዘምሯል። በዕለቱ መ/መንክራት ግርማ ወንድሙ ትምህርት […]

ርስዒ ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ: ሊቀ ጉባኤ አባ ተክለሃይማኖት ወልዱ

በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ቀን ዓመታዊ ክብረ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በርካታ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውሏል። በበዓሉ ዕለቱን በተመለከተ ያሬዳዊ ዝማሬ፣ መንፈሳዊ ትምህርትና ወቅቱን በተመለከተ አባታዊ ምክር በብፁዓን አባቶችና በሊቃውንት ቀርቧል። በሊቃውንት “ይቤላ ሰሎሞን ለማርያም ርግብየ ሠናይት…፤ በገዳሙ የሰንበት ትምህርት ቤት […]

“ልጆቻችሁን ወደ ቤተ ክርስቲያን አምጧቸው” ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ

እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ ቤተ መቅደስ የገባችበት ዓመታዊ ክብረ በዓልና የጻድቁ የአቡነ ዜና ማርቆስ የዕረፍት በዓል በጉራጌ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው በምሁር ኢየሱስ ገዳም በጋራ ተከብሮ ዋለ። ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበዓሉ ላይ ለተገኙት ምእመናን ትምህርት አስተላልፈዋል። ቅዱስ ኢያቄምና ቅድስት ሐና እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሶስት ዓመት ሲሆናት […]

የጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት የዕድሳት ሥራ የሳይት ርክክብ ተካሄደ!!!

በዘመናዊ መልኩ ታድሶ ለአገልግሎት ምቹ የማድረግ ሥራ የተጀመረው የጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት ዝርዝር ጥናቶችን እንዲያጠና በተሰየመው ኮሚቴ አማካኝነት የቅድመ ግንባታ ቴክኒካዊና አስተዳደራዊ ሥራዎችን ሲሠራ ቆይቷል። የጥናት ኮሚቴው የጥምቀት በዓልን መቃረብ ተከትሎ የግንባታ ሥራው በአስቸኳይ እንዲጀመር ማድረግ እንዲቻልና ለግንባታ ሥራው መፋጠን ይረዳ ዘንድ የግብዣ ጨረታ እንዲወጣ የሚቻልበትን ሁኔታን ማመቻቸት እንደሚገባ መክሯል። የጠቅላይ ቤተክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጅ ሊቀ […]

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በአሸባሪው ህውሓት የደረሰበትን ሁለንተናዊ ጉዳት የሚያጠና ቡድን አቋቁሞ ሥራ መጀመሩን ገለጸ !!!

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በተለያዩ ወረዳዎች በአሸባሪው የህውሓት ቡድን በካህናት እና በምእመናን ሕይወት የደረሰውን ጭፍጨፋ፣ እንዲሁም በገዳማትና አድባራቱ የደረሰውን ቁሳዊ ጉዳትና ውድመት የሚያጠና የልኡካን ቡድን አቋቁሞ የጥናት ሥራ መጀመሩን ከጽ/ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል። በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በተሰጠው የሥራ መመሪያ መሠረት የልኡካን ቡድኑ በጦርነቱ የደረሰውን የጉዳት መጠንና ውድመት ለይቶ ከማጥናት ባሻገር […]

በጉራጌ ሀገረ ስብከት ጽ.ቤት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የሰበካ መንፈሳዊ መደበኛ ጉባኤ ባለ14 ነጥብ መግለጫ በማውጣት ተጠናቀቀ !!!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የጉራጌ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የአዲስ አበባና ጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም የቅዱስ ዜና ማርቆስ ዘምሁር መንፈሳዊ ኮሌጅ መሥራች ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ርእሰ መንበርነት ከህዳር 24-25 ቀን 2014 ዓ.ምሲካሄድ የቆየው 17ኛው የሰበካ መንፈሳዊ መደበኛ ጉባኤ ተጠናቋል። የሰበካ መንፈሳዊ መደበኛ ጉባኤ በወልቂጤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የስብሰባ አዳራሽ […]

የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በቆጠር ገድራ መካነ ቅዱሳን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት አንድነት ገዳም ተከብሮ ዋለ!

የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በጉራጌ ሀገረ ስብከት ስር በሚገኘው ቆጠር ገድራ መካነ ቅዱሳን ቅድስት ኪዳነ ምሕረት እና አቡነ ሀብተማርያም አንድነት ገዳም አዳሪ መንፈሳዊ ት/ቤት ተከብሮ ውሏል። ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ክብረ በዓሉን የተመለከተ ትምህርት ሰጥተዋል። ጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ከራሳቸው ፍላጎት ይልቅ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በመፈጸምና በመከተል መልካም ፍሬ […]

“ኢትዮጵያ የእግዚአብሄር ንዋየ ቅድሣት ሀገር ናት !!!” ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ

ዛሬ ህዳር 21 ቀን 2014 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ በተገኙበት በደብረ ምጥማቅ ሠአሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ካቴድራል የእመቤታችን ንግሥ ተከብሮ ውሏል። በአውደ ምህረቱ የካቴድራሉ መምህራን “ሙሴኒ ርዕያ ሀገር ቅድስት የሚለውን እና አባ አቡነ አባ መምህርነ አባ መልከጴዴቅ” የሚለውን ለብፁዕነታቸው በሽብሻቦ አቀርበዋል። የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችም ታቦተ ሕጉ […]

ደቡብ ክልል የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ኮሌጅ ተመረቀ!

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ መመሪያ ሰጭነት በጉራጌ አህጉረ ስብከት ተገንብቶ የተጠናቀቀው መንፈሳዊ ኮሌጅ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በጸሎት ተባርኳል።ኮሌጁም “ዜና ማርቆስ ዘምሁር መንፈሳዊ ኮሌጅ” ተብሎ ተሰይሟል። መንፈሳዊ ኮሌጆች ትውልዱን በመንፈሳዊ ሕይወት ለማነጽ ትልቅ ሚና እንዳላቸው ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ ጠቅሰዋል።አያይዘውም ደቀመዛሙርትን በማሰልጠን ምእመናንን በመንፈሳዊ ትምህርት ተደራሽ ለማድረግ ብዙ መንፈሳዊ ኮሌጆች ለቤተክርስቲያኒቱ እንደሚያስፈልጉም […]

የ 2014 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበርን በተመለከተ በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ውይይት ተካሄደ

ነሐሴ 25 ቀን 2013 ዓ.ም( አዲስ አበባ፡ ኢትዮጵያ )መጪውን የ 2014 ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበርን በተመለከተ በመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን ውይይት ተካሄደ።በመስቀል አደባባይ የሚከበረውን የዘንድሮውን የመስቀል ደመራ በዓል የሚያዘጋጀው የመካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ ቤተክርስቲያን በጥሩ ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ፀሐይ ቀሲስ በቀለ ተሰማ ለብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን