• "እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" መዝ 135:1

  • ”ባህርም አይታ ሸሸች : ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ : ተራሮች እንደ ኮርማዎች ዘለሉ” መዝ 113 ፥ 3

የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት በሥሩ ካሉት አድባራትና ገዳማት ጋር በመሆን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤን እያካሄደ ይገኛል!

በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ሥር ከሚገኙት ከሰባቱ ክፍላተ ከተማ አንዱ የሆነው የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተክህነት ጽ/ቤት ከአድባራቱና ገዳማቱ ጋር በመሆን የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤን እያካሄደ ይገኛል። ጉባኤው እየተካሄደ ያለው በቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን የስብከተ ወንጌል አዳራሽ ነው። ሊ/ት ወንድወሰን ገ/ሥላሴ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ በጉባኤው ላይ ለተገኙት “የእንኳን ደህና መጣችሁ” መልእክት […]

“ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ለኢትዮጵያ የተሰጡ ቅዱስ አባታችን ናቸው”… ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ

የጻድቁ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት ዓመታዊ የልደት ክብረ በዓል በመርካቶ ደብረ አሚን አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱን ጨምሮ በርካታ ካህናትና ምእመናን በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት ተከብሯል። የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ በመርካቶ ደብረ አሚን […]

የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ለ53 አህጉረ ስብከት የ106 ሚልዮን ብር ድጋፍ አደረገ

በብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ የሚመራው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ለ53 አህጉረ ስብከት የ106 ሚልዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን አሳውቋል። በሀገረ ስብከቱ ድጋፍ የተደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥቅምት 16 ቀን 2014 ዓ/ም በወሰነው ውሳኔ መሠረት መሆኑን ተገልጿል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በጥቅምቱ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባው ላይ በቅቱን ተከትሎ በተለያየ ምክንያት ችግር ለደረሰባቸውና የምጣኔ […]

የቤተ ክርስቲያን ታላላቅ አባቶችን በማፍራት የሚታወቀው የፈለገ ቅዱሳን ሰ/ት/ቤት 43ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን አከበረ!

የአዲስ አበባ እና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅን ጨምሮ ታላላቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን ያፈራው የወልቂጤ ደ/ፅ/ቅ/ማርያም ፈለገ ቅዱሳን ሰ/ት/ቤት 43ኛ ዓመት የምሥረታ በዓሉን ከታኅሣሥ 15 እስከ 17 ባሉት ቀናት ውስጥ በደማቅ ሁኔታ አክብሯል። በመርሐ ግብሩ ላይ የሦስት ቀን የዐውደ ምኅረት ጉባኤ እና በከተማው ለሚገኙ የሰ/ ት/ቤቶች የአገልግሎት ሥልጠና ተሰጥቷል። በተያያዘም የምክክር […]

የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በድምቀት ተከብሮ ዋለ

የሊቀ መላእክት የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል በመንበረ መንግሥት ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የአዲስ አበባና የጉራጌ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና በርካታ ምእመናን በተገኙበት በድምቀት ተከብሮ ውላል። በበዓሉ በሊቃውንት ‘ወረደ መልአክ ሊቀ መላእክት ኃበ ሠለስቱ ደቂቅ’ የሚል ያሬዳዊ ዝማሬ ሲቀርብ፣በገዳሙ የሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ‘ገብርኤል ምልአኒ መንፈሰ ልሳን፣ ለተናብቦ መንፈሰ […]

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ አሸባሪው ህወሓት በወልዲያ በርካታ ንፁሐንን በመግደልና ንብረት በመዝረፍ ከፍተኛ በደል መፈፀሙን አስታወቁ !!!

የሰሜንና የደቡብ ወሎ እንዲሁም የከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ አሸባሪው ህወሓት በወልዲያ በርካታ ንፁሐንን መግደሉንና በንብረት ላይ ዘረፋ እና ውድመት መፈፀሙን አስታወቁ። ብፁዕነታቸው አሸባሪው ቡድን በወልዲያ ከተማ በቆየባቸው ጊዜያት የከተማው ነዋሪ እህል ፣ መድኃኒት እና አስፈላጊ ነገሮችን ሳያገኝ መቆየቱን ገልፀዋል። በተጨማሪም ከግለሰብ ኪስ ጀምሮ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማትን መዝረፋቸውን እና ማውደማቸውን  […]

የሰሜን አሜሪካ ማኀበረ ካህናት ለቤተክርስቲያንና ለሀገር ዘረፈ ብዙ አገልግሎት እያበረከተ መሆኑ ተገለጸ!!!

በሰሜን አሜሪካ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት የሚያገለግሉ ካህናት “የሰሜን አሜሪካ ማኅበረ ካህናት ” በሚል ኅብረት መሥርተው ሀገራቸውና ቤተክርስቲያናቸውን በሁለንተናዊ መልኩ እያገለገሉ ይገኛሉ። ማኅበሩ የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን መገደል ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል ለተጎዱ ካህናትን ምዕመናን ዕርዳታ ለማድረግ ያሰባሰበውን ገንዘብ በአግባቡ ለተጎጂዎች በማሰራጨት የፕሮጀክቱን መዝጊያ ሥነ ሥርዓት እንዲሁም ወቅታዊው የሀገራችንንና የቤተ ክርስቲያንን ሁኔታ አስመልክቶ የተዘጋጀውን መርሐ ግብር  […]

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ለሦስት ቀናት ሲያካሂድ የሰነበተው ጸሎተ ፍትሐትና ምሕላ ተጠናቀቀ!!!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰሜን ሽዋ ሀገረ ስብከት በኅልውና ዘመቻ ለሀገርና ለወገን በመዋደቅ ለተሰው የጸጥታ አባላትና በጦርነቱ የተነሣ ሕይወታቸውን ላጡ ምእመናን በደብረ ብርሃን ከተማ አጼ ዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ ከታኅሣሥ 5 -7 ለሦስት ቀናት ሲያካሂድ የሰነበተው ጸሎተ ፍትሐትና ጸሎተ ምሕላ ተጠናቅቋል:: ለሦስት ቀናት የተካሄደውን ጸሎተ ፍትሐትና ምሕላ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ እና በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ […]

የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በሆስፒታል ለሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች የሚውል 400 ሽህ ብር የሚገመት ድጋፍ አደረገ !!!

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን የባህር ዳር ሀገረ ስብከት በባህር ዳር ፈለገ ሕይወት ሆስፒታል ለሚገኙ የፀጥታ ኃይሎች የሚውል 400 ሽህ ብር የሚገመት ድጋፍ አድርጓል፡፡ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አብርሃምንጨምሮ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች በሆስፒታሉ በመገኘት ታካሚ የፀጥታ አካላትን ጎብኝተዋል፣ የህክምና መስጫ ግብአቶችንና አልባሳትንም ለሆስፒታሉ አስረክበዋል። በድጋፍ ርክክብ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ብፁዕነታቸው […]

ማስታወቂያ

አስተያየቶች

    በፌስቡክ ያግኙን